ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ

ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ

ጣቢያው የተቋሙን የስድስት ወራት አፈጻጸም ገምግሟል።

በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ስር ከሚተዳደሩት አንዱ የሆነው የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በሚገኙ ሁለት ዞኖች አማርኛ ቋንቋን ጨምሮ በአምስት የብሔረሰብ ቋንቋዎች አስተማሪ፣ አዝናኝና አሳዋቂ የሆኑ ዜናና ፕሮግራሞችን በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥንና በማህበራዊ ሚዲያ መረጃ ለህብረተሰቡ በማድረስ ላይ ይገኛል።

በተለይም በህብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመለየት በሚመለከታቸው አካላት ምላሽ እንዲያገኙ ከማድረግ አንጻር ተቋሙ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ተመላክቷል።

ተቋሙ የስድስት ወራት አፈጻጸሙን በገመገመበት ወቅት የተቋሙ ስራ አስኪያጅ አቶ ትእዛዙ ኪንጫ፤ ተቋሙ ወቅታዊና ሚዛናዊ መረጃ ለህብረተሰቡ በማድረስ በኩል የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።

በአፈፃፀም ሂደት የተገኙ ጥንካሬዎችን በማጠናከር ጉድለቶችን በማረም በቀጣይ ስድስት ወራት የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ መዘጋጀት እንደሚገባም ጠቁመዋል።

የተቋሙ ባለሙያዎች በበኩላቸው ተቋሙ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያ ጭምር በማሰራጨት ህብረተሰቡን የመረጃ ተጠቃሚ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው የገበያ ልማት ስራዎችን በማጠናከር በጋራ የገቢ አቅምን ማሳደግ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

ዘጋቢ: አብዮት በቀለ – ከሚዛን ጣቢያችን