አስቶንቪላ ማርከስ ራሽፎርድን እና ማርኮ አሴንሲዮን ሊያስፈርም ነው
የእንግሊዙ ክለብ አስቶንቪላ ማርከስ ራሽፎርድን ከማንቸስተር ዩናይትድ እንዲሁም ማርኮ አሴንሲዮን ከፒኤስጂ በውሰት ለማስፈረም ከስምምነት ላይ መድረሱ ተነግሯል።
ከህዳር ወር አንስቶ በሩበን አሞሪም በሚመራው የቀያይ ሰይጣኖች ዋናው ቡድን ስብስብ ውስጥ መካተት ያልቻለው ማርከስ ራሽፎርድ ዝውውሩን ለማጠናቀቅ ወደ አስቶንቪላ እንደሚያቀናም ተነግሯል።
በማንቸስተር ዩናይትድ እስከ 2028 ድረስ የሚያቆየው ኮንትራት ላለው ማርከስ ራሽፎርድ በውሰት ቆይታውም አስቶንቪላ 70 በመቶ የሚሆነውን ሳምንታዊ የደመወዝ ክፍያ ይከፍላል ተብሏል።
የካሪንግተን አካዳሚ ፍሬ የሆነው ማርከስ ራሽፎርድ በትያትር ኦፍ ድሪምስ እስካሁን ለዋናው ቡድን ከ400 በላይ ጨዋታዎችን አከናውኖ 138 ጎሎችን ከመረብ አሳርፏል።
በተጨማሪም በአሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ የሚመራው አስቶንቪላ እስፔናዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ማርኮ አሴንሲዮን ከፒኤስጂ እስከ ውድድር ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በሚቆይ የውሰት ውል ለማስፈረም ተስማምቷል።
አስቶንቪላ ለቀድሞው የሪያል ማድሪድ ተጫዋች በፒኤስጂ የሚከፈለውን ሳምንታዊ የደመወዝ ክፍያ ሙሉ በሙሉ ይሸፍናል ተብሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 አሸነፈ
ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ የምስክር ወረቀት ተሰጠው