የጥንቃቄ መልዕክት-ዶክተር ደግነት አማዶ (የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ስፔሻሊስት )
በዶ/ር ቦጋለች መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል” የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር ደግነት አማዶ ቅባትና ስብ የበዛባቸው ምግቦችን ማብዛት ጉዳቱ የከፋ ነው ይላሉ ፡፡
ከቅባት ምግቦች በተጨማሪ አትክልቶችና ፍራፍሬዎን በስብጥር መመገብ እንደሚገባም በማለት ይመክራሉ ።
በጾም ወራት ለተወሰነ ጊዜ ከፍስግ ምግቦች እርቀው የቆዩ ግለሰቦች ቶሎ ለቅባታማ ምግቦች በሚጋለጡበት ጊዜ ለተለያዩ ተላላፊ ላልሆኑ የጤና እክሎች ሊገጥሟቸው እንደሚችል የሚናገሩት ዶ/ር ደግነት ቅባትና ስብ የበዘባቸውን ምግቦች ማዘውተር ለደም ግፊት፣ ለልብ ህመም ፣ለኮሌስትሮል መጨመር ለጨጓራ ህመምና ለመሳሰሉት በሽታዎች ሊያጋልጥ እንደሚችል ዶክተር ደግነት አብራርተዋል ።
የሀገራችን የስብጥር አመጋገብ ባህል አነስተኛ ነው ያሉት ዶ/ር ደግነት የአትክልትና ፍራፍሬ ገበታን በማብዛት ሊከሰቱ የሚችሉ የጤና እክሎችን መከላከል እንደሚገባም አሳስበዋል ።
ዘጋቢ : መልካሙ ታፈሠ -ከሆሳዕና ጣቢያችን።

More Stories
በክልሉ በ5ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከ6 መቶ ሺ በላይ ህፃናት ተጠቃሚ ይሆናሉ
በክልሉ 5ኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻው በክልሉ ከ 1.1ሚሊየን በላይ ህፃናት የክትባት መርሐግብሩ ተጠቃሚ ይሆናሉ
በኮንታ ዞን አመያ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የእናቶች እና ህፃናትን ሞት ለመቀነስ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ