የጥንቃቄ መልዕክት-ዶክተር ደግነት አማዶ (የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ስፔሻሊስት )
በዶ/ር ቦጋለች መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል” የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር ደግነት አማዶ ቅባትና ስብ የበዛባቸው ምግቦችን ማብዛት ጉዳቱ የከፋ ነው ይላሉ ፡፡
ከቅባት ምግቦች በተጨማሪ አትክልቶችና ፍራፍሬዎን በስብጥር መመገብ እንደሚገባም በማለት ይመክራሉ ።
በጾም ወራት ለተወሰነ ጊዜ ከፍስግ ምግቦች እርቀው የቆዩ ግለሰቦች ቶሎ ለቅባታማ ምግቦች በሚጋለጡበት ጊዜ ለተለያዩ ተላላፊ ላልሆኑ የጤና እክሎች ሊገጥሟቸው እንደሚችል የሚናገሩት ዶ/ር ደግነት ቅባትና ስብ የበዘባቸውን ምግቦች ማዘውተር ለደም ግፊት፣ ለልብ ህመም ፣ለኮሌስትሮል መጨመር ለጨጓራ ህመምና ለመሳሰሉት በሽታዎች ሊያጋልጥ እንደሚችል ዶክተር ደግነት አብራርተዋል ።
የሀገራችን የስብጥር አመጋገብ ባህል አነስተኛ ነው ያሉት ዶ/ር ደግነት የአትክልትና ፍራፍሬ ገበታን በማብዛት ሊከሰቱ የሚችሉ የጤና እክሎችን መከላከል እንደሚገባም አሳስበዋል ።
ዘጋቢ : መልካሙ ታፈሠ -ከሆሳዕና ጣቢያችን።

More Stories
በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የደቡብ ማዕከል ድጋፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በጉራፈርዳ ወረዳ ሩዝ ያመረቱ አርሶ አደሮች ምርታማ መሆናቸውን ገለፁ
በክልሉ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎትን ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ለሆኑ እናቶችና ሴቶች ተደራሽ በማድረግ ጤናቸው እንዲጠበቅ በትኩረት መሠራቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለፀ
የነበሩ ችግሮች እየተቀረፉ በመምጣታቸው የተሻለ የጤና አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን በከምባታ ዞን አንዳንድ የዶዮገና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተገልጋዮች ተናገሩ