የጥንቃቄ መልዕክት-ዶክተር ደግነት አማዶ (የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ስፔሻሊስት )
በዶ/ር ቦጋለች መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል” የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር ደግነት አማዶ ቅባትና ስብ የበዛባቸው ምግቦችን ማብዛት ጉዳቱ የከፋ ነው ይላሉ ፡፡
ከቅባት ምግቦች በተጨማሪ አትክልቶችና ፍራፍሬዎን በስብጥር መመገብ እንደሚገባም በማለት ይመክራሉ ።
በጾም ወራት ለተወሰነ ጊዜ ከፍስግ ምግቦች እርቀው የቆዩ ግለሰቦች ቶሎ ለቅባታማ ምግቦች በሚጋለጡበት ጊዜ ለተለያዩ ተላላፊ ላልሆኑ የጤና እክሎች ሊገጥሟቸው እንደሚችል የሚናገሩት ዶ/ር ደግነት ቅባትና ስብ የበዘባቸውን ምግቦች ማዘውተር ለደም ግፊት፣ ለልብ ህመም ፣ለኮሌስትሮል መጨመር ለጨጓራ ህመምና ለመሳሰሉት በሽታዎች ሊያጋልጥ እንደሚችል ዶክተር ደግነት አብራርተዋል ።
የሀገራችን የስብጥር አመጋገብ ባህል አነስተኛ ነው ያሉት ዶ/ር ደግነት የአትክልትና ፍራፍሬ ገበታን በማብዛት ሊከሰቱ የሚችሉ የጤና እክሎችን መከላከል እንደሚገባም አሳስበዋል ።
ዘጋቢ : መልካሙ ታፈሠ -ከሆሳዕና ጣቢያችን።
More Stories
በክትባት ዘመቻው 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ህፃናትን ይከተባሉ-የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ
የታርጫ አጠቃላይ ሆስፒታል ለተገልጋዮች የተሻለ የሕክምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ተገለፀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቀቤና ልዩ ወረዳ የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ሊካሄድ ነው