አትሌት ደዊት ወልዴ እና ሩቲ አጋ በዢያሜን ማራቶን የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል አሸነፉ
በቻይና ዢያሜን በተካሄደ የ2025 የማራቶን ውድድር አትሌት ዳዊት ወልዴ እና ሩቲ አጋ የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል አሸንፈዋል።
በወንዶች ማራቶን አትሌት ዳዊት ወልዴ 2 ሰዓት ከ06 ደቂቃ ከ06 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት የቦታውን ክብረወሰን በመስበር ማሸነፍ ችሏል።
በውድድሩ ሌላኛው ኢትዮጵያዊው አትሌት አሰፋ ቦኪ በ26 ሴኮንዶች ተቀድሞ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል።
በሴቶች ማራቶን ደግሞ አትሌት ሩቲ አጋ 2 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ46 ሴኮንድ በተመሳሳይ የቦታውን ክብረወሰን በመስበር አሸንፋለች።
እንዲሁም አትሌት ጉተሚ ሾኔ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ11 ሴኮንድ 2ኛ፣አትሌት ፍቅርተ ወረታ 2፡23፡15 ሴኮንድ 3ኛ በመውጣት ተከታትለው በመግባት ማሸነፍ ችለዋል።
ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል