ከ800 ሺህ ሊትር በላይ ዘይት ማሰራጨቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ
ሀዋሳ፡ ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ከ800 ሺህ ሊትር በላይ የፓልም ዘይት በክልሉ ለሚገኙት ዞኖች ማሰራጨቱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ምክትልና የንግድ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አምዴ ፋሪስ እንደገለፁት በሚቀጠሉት ሳምንታት እንደ ክልልም ሆነ እንደሀገር ከሚከበሩ ሁለት ሐይማኖታዊ በዓላት መካከል የልደትና ጥምቀት በዓላት መኖራቸውን ጠቁመው፥ በበዓላት ወቅት ህዝቡ አዘውትሮ ከሚጠቀምባቸው ምርቶች መካከል የምግብ ዘይት አንዱ በመሆኑ በክልሉ ለሚገኙት 6ቱ ዞኖች በሁለት ዙር 858 ሺህ 400 ሊትር ዘይት በሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት በኩል እንዲሰራጭ መደረጉን ተናገረዋል።
ከፍጆታ ምርቶች ጋር ተያይዞ በምግብ ዘይት ላይ መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን የገለፁት አቶ አምዴ፥ በድጎማ የሚቀርቡ ምርቶችን ከገበያ የማስገባትና ገበያውን የማረጋጋት ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በተለይም ከስኳር ጋር ተያይዞ በሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት በኩል ከኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን እንዲቀርብ እየተደረገ መሆኑን ኃላፊው አውስተዋል።
በነፃ ገበያ ስርዓት የሚቀርብ የምግብ ዘይትና ስኳር ምርቶች አቅርቦቱን ለማሻሻል ከጅምላ አቅራቢዎች ጋር ውይይት እንዲደረግ አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራ እንደሚገኝም አቶ አምዴ አሰረድተዋል።
በመንግስት ድጎማ የሚቀርቡ የምግብ ዘይት ምርቶች ለተጠቃሚው ህብረተሰብ በተገቢውና በፍትሃዊነት እንዲደርስ በማድረግ በኩል በየደረጃ የሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ኃላፊው አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ አብዲሳ ዮናስ – ከሚዛን ጣቢያችን


More Stories
የሀለባ ዞን ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ3 ቢልዮን 293 ሚልዮን ብር ባለይ በጀት አጸደቀ
መስራት እየቻሉ የገንዘብ እጥረት የገጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን ችግሮች ለመፍታት የህብረት ስራ ማህበራት ሚና ቀላል አለመሆኑ ተገለጸ
በስልጤ ልማት ማህበር ለ3ኛ ጊዜ በተዘጋጀው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ከሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር የተሰበሰቡ የአካባቢው ተወላጆች በዞኑ በሚገኙ የላንፉሮ ወረዳና ጦራ ከተማ አስተዳደር ችግኞችን ተክለዋል ።