ሀዋሳ፡ የካቲት 04/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ”ሃይማኖቶች ለሰላም ለመከባበር እና ለአንድነት” በሚል መሪ ቃል ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሆሳዕና ከተማ የሚካሄደው የሰላም ኮንፍራንስ ከሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛል።
በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር እና የዕለቱ የክብር እንግዳ እንደሻው ጣሰው(ዶ/ር)፣ ብፁዕ አቡና ህርያቆስ የአዲስ አበባና ሀድያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ፓትርያርኩና የኢሃተጉ የበላይ ጠባቂ ተወካይ፣ ክቡር ሽይኽ አብዱልከሪም ሽይኽ በድረዲን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንትና የፕሬዝዳንቱና የኢሃተጉ የበላይ ጠባቂ ተወካይ፣ ክቡር ቄስ ደረጄ ጀምበሩ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ከውንስል ፕሬዚዳንትና የኢሃተጉ የበላይ ጠባቂ ተወካይ፣ ብፁዕ አቡነ ስዩም ፍራንሷ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የብፁህ ካርዲናልና የኢሃተጉ የበላይ ጠባቂ ተወካይ፣ ፓስተር ታደሠ አዱኛ የኢትዮጵያ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንትና የኢሃተጉ የበላይ ጠባቂ ተወካይ እንዲሁም የሃይማኖት መሪዎች የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀድያ ዞን እና የሆሣዕና ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ በየነ ሰላሙ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በዞኑ ባለፉት 6 ወራት የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ገለጹ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የክልሉን ሕዝብ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሠራ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለጹ
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ