የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤውን የካቲት 6 እና 7 2018 ዓ.ም እንደሚያካሂድ ተገልጿል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የክልሉን ሕዝብ በልማት እና መልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሠራ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ አብራርተዋል።
የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤውን የካቲት 6 – 7/2018 የሚያካሂድ በመሆኑ መላው የክልሉ ምክር ቤት አባላት እንዲገኙ አፈ ጉባኤው ጥሪ አስተላልፈዋል።
በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት በ6 ወራት በክልሉ በተከናወኑ የልማት እና መልካም አስተዳደር ሥራዎች እና ቀሪ ተግባራት ዙሪያ ጉባኤው የሚመክር መሆኑን የገለጹት አፈ ጉባኤው፤ ጉባኤው በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በቀጥታ ስርጭት የሚተላለፍ በመሆኑ መላው የክልሉ ሕዝብ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን በንቃት እንዲከታተል ዋና አፈ ጉባኤው አሳስበዋል።
ዘጋቢ: ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ