የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከቻን ውድድር ውጪ ሆነ
ሀዋሳ፡ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከ2024 የአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ(ቻን) በሁለተኛ ዙር ማጣሪያ በሱዳን በድምር ውጤት ተሸንፎ ከውድድሩ ውጪ ሆኗል።
ዛሬ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ በሊቢያ ቤንጋዚ በቤኒና ማርትርየስ ስታዲየም የመልስ ጨዋታውን ያከናወነው ብሔራዊ 2ለ1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።
ለሱዳን የማሸነፊያ ግቦችን ሞሲ ኮናቴ በ16ኛው ደቂቃ እና መሐመድ አብዱራህማን በ69ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል።
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ደግሞ ብቸኛዋን ግብ ብርሀኑ በቀለ በ63ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል።
ውጤቱን ተከትሎ ዋልያዉ በድምር ውጤት 4ለ1 ተሸንፎ ማለፍ ሳይችል ቀርቷል።
ዘጋቢ፡ በሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል