ማንቸስተር ሲቲ በአስቶንቪላ ተሸነፈ
በ17ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬርሊግ ማንቸስተር ሲቲ በአስቶንቪላ 2ለ1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።
የአስቶንቪላን የማሸነፊያ ግቦች ጆን ዱራን እና ሞርጋን ሮጀርስ ከመረብ አሳርፈዋል።
ማንቸስተር ሲቲን ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ ፊል ፎደን አስቆጥሯል።
ማንቸስተር ሲቲ እንደ አውሮፓውያኑ ከ2001 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሜዳው ውጪ በ8 ተከታታይ ጨዋታዎች ሁለት እና ከዛ በላይ ተቆጥረውበታል።
ፕሪሚዬር ሊጉ መካሄዱን ሲቀጥል በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ብሬንትፎርድ ከኖቲንግሃም ፎረስት፣ ኢፕሲች ታውን ከኒውካስል ዩናይትድ እንዲሁም ዌስትሃም ዩናይትድ ከብራይተን ይጫወታሉ።
ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ ደግሞ በለንደን ደርቢ ክርስቲያል ከአርሰናል ይፋለማሉ።
በሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል