8 ወራትን ብቻ በሰሜን ለንደን የቆየው አሰልጣኝ

8 ወራትን ብቻ በሰሜን ለንደን የቆየው አሰልጣኝ

የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶትንሃም ዋና አሰልጣኙን ቶማስ ፍራንክን ከሀላፊነት አሰናብቷል።

በውጤት ማጣት ውስጥ የሚገኘው ቶትንሃም ትናንት ምሽት በሜዳው በኒውካስል 2ለ1 ከተሸነፈ በኋላ በማግስቱ ዴንማርካዊውን አሰልጣኝ ማሰናበቱን አሳውቋል።

ክለቡ በፕሪሚዬር ሊጉ ያለፉትን 8 ተከታታይ ጨዋታዎችን ማሸነፍ አልቻለም።

በአሰልጣኙ መሪነት ከመጨረሻዎቹ 17 ሁለቱን ብቻ ያሸነፉት ስፐርሶች ከወራጅ ቀጠናው በአምስት ነጥብ ብቻ እርቀው በሊጉ 16ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

የ52 ዓመቱ አሰልጣኝ ቶትንሃምን  በሁሉም ውድድሮች በ38 ጨዋታዎች 13 ጨዋታዎችን ነው ማሸነፍ የቻሉት።

አሰልጣኝ ቶማስ ፍራንክ ከስምንት ወራት በፊት አሰልጣኝ አንጄ ፖስቴኮግሉን በመተካት ቶትንሃምን መረከባቸው ይታወሳል።

ቶትንሃም ተሰናባቹን አሰልጣኝ ለመተካት ስራዎችን መጀመሩ ተገልጿል።

ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ