በማላጋ የሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት አሸነፉ
በስፔን ማላጋ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል።
ውድድሩን አትሌት አይናለም ደስታ 2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ10 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት በቀዳሚነት አጠናቃለች።
እንዲሁም አትሌት አዳነች መስፍን 2 ሰዓት ከ26 ደቂቃ ከ01 ሴኮንድ የግሏን ምርጥ ሰዓት በማስመዝገብ 2ኛ ሆና ገብታለች።
በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሮጠችው አትሌት ጎጃም ፀጋዬ ደግሞ መውጣት ችላለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 አሸነፈ