በማላጋ የሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት አሸነፉ
በስፔን ማላጋ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል።
ውድድሩን አትሌት አይናለም ደስታ 2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ10 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት በቀዳሚነት አጠናቃለች።
እንዲሁም አትሌት አዳነች መስፍን 2 ሰዓት ከ26 ደቂቃ ከ01 ሴኮንድ የግሏን ምርጥ ሰዓት በማስመዝገብ 2ኛ ሆና ገብታለች።
በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሮጠችው አትሌት ጎጃም ፀጋዬ ደግሞ መውጣት ችላለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሳንቲ ካዞርላ ከእግርኳስ ተጫዋችነት ራሱን አገለለ
ማንቸስተር ሲቲ ኤሊዮት አንደርሰንን በይፋ አስፈረመ
ከጠጠር ሜዳ እስከ ፕሪሚየር ሊግ