በማላጋ የሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት አሸነፉ
በስፔን ማላጋ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል።
ውድድሩን አትሌት አይናለም ደስታ 2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ10 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት በቀዳሚነት አጠናቃለች።
እንዲሁም አትሌት አዳነች መስፍን 2 ሰዓት ከ26 ደቂቃ ከ01 ሴኮንድ የግሏን ምርጥ ሰዓት በማስመዝገብ 2ኛ ሆና ገብታለች።
በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሮጠችው አትሌት ጎጃም ፀጋዬ ደግሞ መውጣት ችላለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
8 ወራትን ብቻ በሰሜን ለንደን የቆየው አሰልጣኝ
ማንቸስተር ዩናይትድ ቶትንሃምን አሸነፈ
አሰልጣኝ ዋሊድ ሬግራጉይ መልቀቂያ አስገቡ