19ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በአልን ለማክበር ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ አርባምንጭ ከተማ የሚመጡ እንግዶች አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል
ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በአሉን ለማክበር ወደ አርባምንጭ ከተማ እየገቡ ለሚገኙ እንግዶች በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቢሮ ኃላፊዎች፣ የዞኑ ዋና አፈ ጉባኤ፣ የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪን ጨምሮ የብርብር ከተማ አስተዳደር እና የወረዳው የስራ ኃላፊዎች እንግዶችን ተቀብለው እያስተናገዱ ይገኛሉ።
እንግዶቹም በተደረገላቸው የሞቀ አቀባበል መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ