19ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በአልን ለማክበር ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ አርባምንጭ ከተማ የሚመጡ እንግዶች አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል
ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በአሉን ለማክበር ወደ አርባምንጭ ከተማ እየገቡ ለሚገኙ እንግዶች በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቢሮ ኃላፊዎች፣ የዞኑ ዋና አፈ ጉባኤ፣ የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪን ጨምሮ የብርብር ከተማ አስተዳደር እና የወረዳው የስራ ኃላፊዎች እንግዶችን ተቀብለው እያስተናገዱ ይገኛሉ።
እንግዶቹም በተደረገላቸው የሞቀ አቀባበል መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ