19ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በአልን ለማክበር ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ አርባምንጭ ከተማ የሚመጡ እንግዶች አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል
ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በአሉን ለማክበር ወደ አርባምንጭ ከተማ እየገቡ ለሚገኙ እንግዶች በጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቢሮ ኃላፊዎች፣ የዞኑ ዋና አፈ ጉባኤ፣ የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪን ጨምሮ የብርብር ከተማ አስተዳደር እና የወረዳው የስራ ኃላፊዎች እንግዶችን ተቀብለው እያስተናገዱ ይገኛሉ።
እንግዶቹም በተደረገላቸው የሞቀ አቀባበል መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ