ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ፤ የክልሉ አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ እና የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ናፊሴ አለማህድ በጋራ በአርባምንጭ ከተማ ክልላዊ የባህልና ቱሪዝም ኤግዚቢሽን እና ፌስቲቫል በይፋ መርቀው አስጀመሩ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 26/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እና የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ናፊሴ አለማህድ በጋራ በአርባምንጭ ከተማ ክልላዊ የባህልና ቱሪዝም ኤግዚቢሽን እና ፌስቲቫል በይፋ መርቀው አስጀምረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ናፊሴ አለማህድ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ጸሐይ ወራሳ ጨምሮ የክልልና የዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፌስቲቫሉን እየጎበኙ ይገኛሉ።
በኤግዚቢሽን እና ፌስቲባሉ በክልሉ የሚገኘ 32ቱ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፤ ባህላቸውን፣ ታሪክና ቅርሳቸውን እንዲሁም የቱሪዝም ሀብቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ ለዘመናት የዘለቀውን ትስስራቸውን ያጠናክሩበታል ተብሏል።
“ሀገራዊ መግባባት፤ ለህብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል 19ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በተለያዩ ሁነቶች በደማቅ ሁኔታ በአርባምንጭ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ