ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ፤ የክልሉ አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ እና የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ናፊሴ አለማህድ በጋራ በአርባምንጭ ከተማ ክልላዊ የባህልና ቱሪዝም ኤግዚቢሽን እና ፌስቲቫል በይፋ መርቀው አስጀመሩ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 26/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እና የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ናፊሴ አለማህድ በጋራ በአርባምንጭ ከተማ ክልላዊ የባህልና ቱሪዝም ኤግዚቢሽን እና ፌስቲቫል በይፋ መርቀው አስጀምረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ናፊሴ አለማህድ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ጸሐይ ወራሳ ጨምሮ የክልልና የዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፌስቲቫሉን እየጎበኙ ይገኛሉ።
በኤግዚቢሽን እና ፌስቲባሉ በክልሉ የሚገኘ 32ቱ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፤ ባህላቸውን፣ ታሪክና ቅርሳቸውን እንዲሁም የቱሪዝም ሀብቶቻቸውን ከማስተዋወቅ ባለፈ ለዘመናት የዘለቀውን ትስስራቸውን ያጠናክሩበታል ተብሏል።
“ሀገራዊ መግባባት፤ ለህብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል 19ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በተለያዩ ሁነቶች በደማቅ ሁኔታ በአርባምንጭ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ሀገራዊ ምክክር፤ የመደማመጥ፣ የመግባባትና የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ነው!
ከ23 ሚሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተገለጸ
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።