19ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ያለአንዳች ፀጥታ ችግር ተከብሮ እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ተደርጓል – የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን
ሀዋሳ፡ ሕዳር 25/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 19ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ያለአንዳች ፀጥታ ችግር ተከብሮ እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት መደረጉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ይህንን አስመልክቶ ለሚዲያ አካላት መግለጫ ሰጥቷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍሰሀ ጋረደው በሰጡት መግለጫ፤ 19ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ተከብሮ በሠላም እንዲጠናቀቅ በፀጥታ አካላት በቂ ዝግጅት መደረጉን አብራርተዋል።
በመላው ሀገሪቱ እንግዶች በዓሉን ለማክበር በሚመጡበት ወቅት የፀጥታ ችግር እንዳይኖር ከአጎራባች ክልሎች ጋርም በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የፌደሬሽን ምክር ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ በላይ መርሻ በበኩላቸው፤ እየተከበረ የሚገኘው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በሠላም እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላትን ጨምሮ የፀጥታ ሀይሉ በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል።
በዓሉ ተከብሮ እስከሚጠናቀቅ የፀጥታ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።
ዘጋቢ፡ እንጃ ገልሲሞ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ