19ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ያለአንዳች ፀጥታ ችግር ተከብሮ እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ተደርጓል – የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን
ሀዋሳ፡ ሕዳር 25/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 19ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ያለአንዳች ፀጥታ ችግር ተከብሮ እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት መደረጉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ይህንን አስመልክቶ ለሚዲያ አካላት መግለጫ ሰጥቷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍሰሀ ጋረደው በሰጡት መግለጫ፤ 19ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ተከብሮ በሠላም እንዲጠናቀቅ በፀጥታ አካላት በቂ ዝግጅት መደረጉን አብራርተዋል።
በመላው ሀገሪቱ እንግዶች በዓሉን ለማክበር በሚመጡበት ወቅት የፀጥታ ችግር እንዳይኖር ከአጎራባች ክልሎች ጋርም በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የፌደሬሽን ምክር ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ በላይ መርሻ በበኩላቸው፤ እየተከበረ የሚገኘው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በሠላም እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላትን ጨምሮ የፀጥታ ሀይሉ በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል።
በዓሉ ተከብሮ እስከሚጠናቀቅ የፀጥታ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።
ዘጋቢ፡ እንጃ ገልሲሞ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/