የቡርጂ ዞን ሶያማ ከተማ የበጋ በጎ ፈቃድ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በተለያዩ ስፖርታዊ ዝግጅቶች ተጀመረ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 23/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቡርጂ ዞን ሶያማ ከተማ የበጋ በጎ ፈቃድ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በተለያዩ ስፖርታዊ ዝግጅቶች ተጀምሯል፡፡
ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የሶያማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ፍስሃ አድማሱ ባደረጉት ንግግር፤ የከተማው ወጣት የአካል ብቃቱን እና የስፖርት ችሎታውን ለማሳደግ በስፖርታዊ ውድድሮች ላይ መሳተፍ እንዳለበት አመላክተዋል።
በሶያማ ከተማ ደረጃ ብቁ እና በስነ-ምግባር የታነፀ ወጣት ለማፍራት ቃል መገባቱን ያስታወሱት ከንቲባው፤ ውድድሩ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ከተማ አስተዳደሩ ምቹ ሁኔታ የመፍጠሩን ስራ አጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት።
በበጋ ወቅት ከሚሰሩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መካከል አንዱ የሆነው የእግር ኳስ ጨዋታ በአጠቃላይ በአዋቂ 4 በታዳጊ 6 በድምሩ 10 ቡድኖች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ታውቋል።
በመርሃ ግብሩ የዞን፣ የሶያማ ዙሪያ ወረዳ እንዲሁም የሶያማ ከተማ አስተዳደር አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታዳሚ ሆነዋል።
ዘጋቢ፡ ወርቅአገኘሁ ወልደየስ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/