በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 19ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ክልላዊ የማጠቃለያ ፕሮግራም እየተካሄደ ነዉ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 23/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ሀገራዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 19ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ክልላዊ የማጠቃለያ ፕሮግራም በክልሉ የብሔረሰቦች ምክር ቤት መቀመጫ በሆነዉ የም ዞን ሳጃ ከተማ እየተከበረ ነዉ።
በበዓሉ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻዉ ጣሰዉ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬን ጨምሮ የክልል፣ የዞንና ልዩ ወረዳ አመራሮች፣ የአጎራባች ክልል ተወካዮች፣ የሐይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ድልነሳዉ ታደሰ

                
                                        
                                        
                                        
                                        
More Stories
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ
ከ2 ሺህ በላይ አዲስ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማሰልጠን መታቀዱን የሆሳዕና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አስታወቃ