ለውጡና የለውጡ ፍሬዎች !!!
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ
ብልጽግና ፓርቲ ነባሮቹን ፖለቲካዊ ዕሤቶች በሚያጎለብትና የፖለቲካ ስብራቶቻችንን በሚጠግን መልኩ ተመሥርቷል፡፡ ይሄም የለውጡ አንዱ ፍሬ ነው፡፡
የብልጽግና መመሥረት የዳርና የመሐል፤ ዋና እና አጋር፣ አርብቶ አደርና አርሶ አደር፤ ተራማጅና አድኃሪ፤ ጠላትና ወዳጅ፣ ወዘተ. የሚባሉትን ግንቦች በማፍረስ በሐሳብ ላይ ብቻ የተመሠረተ የፖለቲካ አደረጃጀትን ፈጥሯል፡፡
የሐሳብ ልዩነቶችን እንደ ጌጥና ዕሴት በመውሰድ ተፎካካሪዎቹን በጠላትነት አይፈርጅም፡፡ በኢትዮጵያዊ ዕሴቶች ላይ በመመሥረት፣ ከሌሎች ሐሳቦች በመማር፣ በገቢር ነበብ መንገድ ይጓዛል እንጂ የርዕዮተ ዓለም እሥረኛ አይደለም፡፡
ለአንድ አካባቢ ወይም ብሔር የቆመ ሳይሆን ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ያለው የሐሳብ ፓርቲ ነው፡፡ ይሄም የኢትዮጵያን የፖለቲካ መልክአ ምድር የለወጠ የለውጥ ፍሬ ነው፡፡
More Stories
የካፋ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ዝግጅት ላይ ውይይት እያካሄደ ነው
በወላይታ ዞን አረካ ከተማ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቁን ተከትሎ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት ማጠቃለያ ሴክተር ጉባኤውን በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ነው