በመኸር እርሻ ከተዘራው ሰብል 53 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ወደ ጎተራ ገብቷል
በ2016/17 ዓ.ም በምኸር እርሻ በዘር ከተሸፈነ 20 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ከሰባት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ምርት የመሰብሰብ ስራ ተሰርቷል።
ከተሰበሰበው ሰባት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሄክታር መሬት 53 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ወደ ጎተራ ገብቷል።
በግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ኢሳያስ ለማ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በ2016/17 መኸር እርሻ በዘር ከተሸፈነ 20 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ ሰባት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ያለወ ሰብል ተሰብስቧል። ከዚህም 53 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ወደ ጎተራ ገብቷል፡፡
በዘር ከተሸፈነ 20 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ 12 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ያለው ሰብል ለመሰብሰብ ደርሷል ያሉት መሪ ስራ አስፈፃሚው ከዚህም ስድስት ነጥብ ስምንት ሚሊየን በሰው ሀይል፤ 360 ሺህ ሄክታሩን በኮባይነር የመሰብሰብ ስራ ተከናውኗል፡፡ ወደ አምስት ሚሊዮን የሚጠጋ ሄክታር መሬት አለመሰብሰቡን ገልጸዋል።
ከ2016/17 ዓም የምኸር እርሻ 615 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቀም ጠቁመዋል፡፡

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ