የትምህርት ቤት አመራሮች ትውልድን በመቅረጽም ሆነ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ረገድ የማስተባበር፣ ክትትልና ድጋፍ የማድረግና አስተማማኝ የሆነ የክፍል ውስጥ ትምህርትና ውጤት እንዲመዘገብ በትኩረት እንዲሰሩ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው አሳሰቡ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የትምህርት ቤት አመራሮች ትውልድን በመቅረጽም ሆነ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ ረገድ የማስተባበር፣ ክትትልና ድጋፍ የማድረግና አስተማማኝ የሆነ የክፍል ውስጥ ትምህርትና ውጤት እንዲመዘገብ በትኩረት እንዲሰሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው አሳስበዋል።
በክልሉ ለሚገኙ የትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራኖች “የትምህርት ቤት አመራሮች ብቃት፤ ለላቀ የትምህርት ጥራት” በሚል መሪ ሀሳብ የአቅም ግንባታ ስልጠና በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ መሰጠት ተጀምሯል።
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው አክለውም የትምህርት አመራሮች የትምህርት ስብራትን ለማሻሻል እየተተገበረ ያለውን የትምህርት ጥራት ማሻሻያ በተገቢው በተግባር በማዋል የትውልድ ግንባታ ላይ በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
በአቅም ግንባታ ስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰውን ጨምሮ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዳዊት ሃዬሶ እንዲሁም ሌሎች አካላት ተገኝተዋል።
የአቅም ግንባታ ስልጠናው ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
ዘጋቢ: ወንድወሰን ሽመልስ
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ