የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን እንደሚያረጋግጥ ተገለፀ
በደቡብ ኦሞ ዞን ኛንጋቶም ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት መሪነት በወረዳዉ ማዕከል ካንጋቲን ከተማ ”ምርታማነት ለቤተሰብ ብልፅግና በአዲስ እመርታ ገፅታ” በሚል መሪ ቃል በወቅታዊ የግብርና ስራዎች ዙርያ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የወረዳዉ ምክትል አስተዳዳሪና ቆላማና መስኖ አካባቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ እንጂነር ሎካሎቦንግ ሎሴኮና ባደረጉት ንግግር፤ የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ያረጋግጣል ብለዋል።
አያይዘዉም ምርታማነትን ማሳደግ ማለት በተግባር ተተግብሮ ዉጤት የሚያመጣ መሆን እንዳለበት ከመናገራቸዉ ባለፈ እንደወረዳ በዘርፉ በየቀበሌዉ ወጣ ገባ አፈፃፀምና ትግበራ የሚስተዋል በመሆኑ ሁሉም ቀበሌያት ላይ የትግበራው ወጥነት ሊኖር እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመድረኩ ከተሳተፉት መካከል አርብቶ አደር አርቦ ናሞያ፣ ሎሮት ቃሌም እና ሌሎችን ጨምሮ ከድህነት ለመላቀቅ መንግስት የሚያወርዳቸዉን ተልዕኮዎች ተቀብለዉ በአግባቡ ቢተገብሩ ተጠቃሚ እንደሚያደርጋቸዉ አስተያየታቸዉን ሰጥተዋል።
በመድረኩ የመወያያ ሰነድ በወረዳዉ ግብርና ጽ/ቤት ሐላፊ በአቶ ታደለ በቀለ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን በሰነዱ ከቀረቡ ትኩረት ከሚሹ ጉዳዮች ውስጥ ለግብርናዉ ዘርፍ የባለድርሻ አካላት ትኩረት ማነስ፣ የመካናይዜሽን ማሽኖች ሲበላሹ ወቅታዊ ጥገና አድርጎ ወደስራ አለማስገባት፣ የቀበሌ ግብርና ባለሙያዎች የመንግስት ስራ ሰዓትን አክብሮ አለመስራት፣ የደን ጭፍጨፋ መበራከት፣ የግብርና ቴክኖሎጂን በአግባቡ አለመጠቀም የሚሉት ሐሳቦች ይገኙበታል።
በመድረኩ የሚመለከታቸዉ የወረዳ ስራ አስፈፃሚዎች፣ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች፣ ከየቀበሌያቱ የተዉጣጡ የግብርና ባለሙያዎች እና የቀበሌ ሊቃነ መናብርት ተሳትፊዎች ናቸዉ።
ተመሳሳይ መድረኮች በተዋረድ በቀበሌ ደረጃ እንደሚተገበሩም ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ ወንድማገኝ በቀለ – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በማር ምርት ዘርፍ 360 ሺህ ሥራ አጥ ወጣቶችን በማደራጀት ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሠራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ አስታወቁ
በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ ለ2መቶ 50 ድጋፍ ለሚሹ አቅመ-ደካማና አረጋውያን ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር ተደረገ
በበዓላት ሰሞን የትራንስፖርት እጥረት፣ የታሪፍ ጭማሪና የትራፊክ አደጋ እንዳይከሰት እየሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን መንገድና ትራንስፖርት መምሪያ ገለፀ