የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን እንደሚያረጋግጥ ተገለፀ
በደቡብ ኦሞ ዞን ኛንጋቶም ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት መሪነት በወረዳዉ ማዕከል ካንጋቲን ከተማ ”ምርታማነት ለቤተሰብ ብልፅግና በአዲስ እመርታ ገፅታ” በሚል መሪ ቃል በወቅታዊ የግብርና ስራዎች ዙርያ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የወረዳዉ ምክትል አስተዳዳሪና ቆላማና መስኖ አካባቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ እንጂነር ሎካሎቦንግ ሎሴኮና ባደረጉት ንግግር፤ የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ያረጋግጣል ብለዋል።
አያይዘዉም ምርታማነትን ማሳደግ ማለት በተግባር ተተግብሮ ዉጤት የሚያመጣ መሆን እንዳለበት ከመናገራቸዉ ባለፈ እንደወረዳ በዘርፉ በየቀበሌዉ ወጣ ገባ አፈፃፀምና ትግበራ የሚስተዋል በመሆኑ ሁሉም ቀበሌያት ላይ የትግበራው ወጥነት ሊኖር እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመድረኩ ከተሳተፉት መካከል አርብቶ አደር አርቦ ናሞያ፣ ሎሮት ቃሌም እና ሌሎችን ጨምሮ ከድህነት ለመላቀቅ መንግስት የሚያወርዳቸዉን ተልዕኮዎች ተቀብለዉ በአግባቡ ቢተገብሩ ተጠቃሚ እንደሚያደርጋቸዉ አስተያየታቸዉን ሰጥተዋል።
በመድረኩ የመወያያ ሰነድ በወረዳዉ ግብርና ጽ/ቤት ሐላፊ በአቶ ታደለ በቀለ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን በሰነዱ ከቀረቡ ትኩረት ከሚሹ ጉዳዮች ውስጥ ለግብርናዉ ዘርፍ የባለድርሻ አካላት ትኩረት ማነስ፣ የመካናይዜሽን ማሽኖች ሲበላሹ ወቅታዊ ጥገና አድርጎ ወደስራ አለማስገባት፣ የቀበሌ ግብርና ባለሙያዎች የመንግስት ስራ ሰዓትን አክብሮ አለመስራት፣ የደን ጭፍጨፋ መበራከት፣ የግብርና ቴክኖሎጂን በአግባቡ አለመጠቀም የሚሉት ሐሳቦች ይገኙበታል።
በመድረኩ የሚመለከታቸዉ የወረዳ ስራ አስፈፃሚዎች፣ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች፣ ከየቀበሌያቱ የተዉጣጡ የግብርና ባለሙያዎች እና የቀበሌ ሊቃነ መናብርት ተሳትፊዎች ናቸዉ።
ተመሳሳይ መድረኮች በተዋረድ በቀበሌ ደረጃ እንደሚተገበሩም ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ ወንድማገኝ በቀለ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የሀለባ ዞን ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ከ3 ቢልዮን 293 ሚልዮን ብር ባለይ በጀት አጸደቀ
መስራት እየቻሉ የገንዘብ እጥረት የገጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን ችግሮች ለመፍታት የህብረት ስራ ማህበራት ሚና ቀላል አለመሆኑ ተገለጸ
በስልጤ ልማት ማህበር ለ3ኛ ጊዜ በተዘጋጀው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ከሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር የተሰበሰቡ የአካባቢው ተወላጆች በዞኑ በሚገኙ የላንፉሮ ወረዳና ጦራ ከተማ አስተዳደር ችግኞችን ተክለዋል ።