የጂንካ ዩኒቨርሲቲ አዲስ አፈር አልባ የመኖ አመራረት ዘዴን አስተዋወቀ
(Hydrophoncs Green Fodder production technology) በመባል የሚታወቀውና ያለ አፈር በውሃ ብቻ የሚከናወን የመኖ አመራረት ስርዓት ሲሆን አውሮፓን ጨምሮ ሌሎች ሐገራትም የሚጠቀሙበት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ነው።
የተለያዩ የሰብል አይነቶችን በቀላሉ ማምረት የሚያስችለው ይህ ቴክኖሎጂ በእንሰሳት ሀብት ልማት ዘርፍ በተለይም የእንሰሳት ተዋጽኦን ምርታማነት ከፍ በማድረግ ረገድ ያለው አስተዋጾ ከፍተኛ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል።
በዩኒቨርሲቲው የተጀመረው አዲሱ የአፈር አልባ የመኖ አመራረት ስልትን በማህበረሰቡ ለማስፋፋት ይቻል ዘንድ የተደረገ የመስክ ምልከታም ተካሂዷል።
አፈር አልባ የመኖ አመራረት ስርዓቱም በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንትን ዶ/ር ኩሴ ጉድሼ፣ የአስተዳደር ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር አለሙ አይለቴን ጨምሮ ሌሎች ባላድርሻ አካላትም ተጎብኝቷል።
ዘጋቢ ፡ አርሻል አራቦ – ከጂንካ ቅርንጫፍ ጣቢያ
More Stories
የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሥራዎችን ለማጠናከርና ዘርፉን በማሳለጥ በኩል የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመቅረፍ የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ የደቡብ ኦሞ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ገለፀ
ለዜጎች በሶላር ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮረ ስልጠና በመስጠት ዘርፉ ላይ ተጠቃሚነታቸውን ለማጎልበት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አስታወቀ
በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራርን ተግባራዊ በማድረጋቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን በየኪ ወረዳ የኩቢጦ አካባቢ አርሶአደሮች ተናገሩ