የጂንካ ዩኒቨርሲቲ አዲስ አፈር አልባ የመኖ አመራረት ዘዴን አስተዋወቀ
(Hydrophoncs Green Fodder production technology) በመባል የሚታወቀውና ያለ አፈር በውሃ ብቻ የሚከናወን የመኖ አመራረት ስርዓት ሲሆን አውሮፓን ጨምሮ ሌሎች ሐገራትም የሚጠቀሙበት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ነው።
የተለያዩ የሰብል አይነቶችን በቀላሉ ማምረት የሚያስችለው ይህ ቴክኖሎጂ በእንሰሳት ሀብት ልማት ዘርፍ በተለይም የእንሰሳት ተዋጽኦን ምርታማነት ከፍ በማድረግ ረገድ ያለው አስተዋጾ ከፍተኛ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል።
በዩኒቨርሲቲው የተጀመረው አዲሱ የአፈር አልባ የመኖ አመራረት ስልትን በማህበረሰቡ ለማስፋፋት ይቻል ዘንድ የተደረገ የመስክ ምልከታም ተካሂዷል።
አፈር አልባ የመኖ አመራረት ስርዓቱም በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንትን ዶ/ር ኩሴ ጉድሼ፣ የአስተዳደር ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር አለሙ አይለቴን ጨምሮ ሌሎች ባላድርሻ አካላትም ተጎብኝቷል።
ዘጋቢ ፡ አርሻል አራቦ – ከጂንካ ቅርንጫፍ ጣቢያ

More Stories
በክልሉ የተለያዩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚሠራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
አሰልጣኞች ወቅቱ የሚጠይቀውን የቴክኖሎጂ ክህሎት እንዲላበሱ እየተሠራ መሆኑ ተጠቆመ
በቴክኖሎጂ የተካኑ ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት በመሥራት ሀገሪቱን ማበልጸግ እንደሚገባ ተገለጸ