የጂንካ ዩኒቨርሲቲ አዲስ አፈር አልባ የመኖ አመራረት ዘዴን አስተዋወቀ
(Hydrophoncs Green Fodder production technology) በመባል የሚታወቀውና ያለ አፈር በውሃ ብቻ የሚከናወን የመኖ አመራረት ስርዓት ሲሆን አውሮፓን ጨምሮ ሌሎች ሐገራትም የሚጠቀሙበት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ነው።
የተለያዩ የሰብል አይነቶችን በቀላሉ ማምረት የሚያስችለው ይህ ቴክኖሎጂ በእንሰሳት ሀብት ልማት ዘርፍ በተለይም የእንሰሳት ተዋጽኦን ምርታማነት ከፍ በማድረግ ረገድ ያለው አስተዋጾ ከፍተኛ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል።
በዩኒቨርሲቲው የተጀመረው አዲሱ የአፈር አልባ የመኖ አመራረት ስልትን በማህበረሰቡ ለማስፋፋት ይቻል ዘንድ የተደረገ የመስክ ምልከታም ተካሂዷል።
አፈር አልባ የመኖ አመራረት ስርዓቱም በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንትን ዶ/ር ኩሴ ጉድሼ፣ የአስተዳደር ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር አለሙ አይለቴን ጨምሮ ሌሎች ባላድርሻ አካላትም ተጎብኝቷል።
ዘጋቢ ፡ አርሻል አራቦ – ከጂንካ ቅርንጫፍ ጣቢያ
More Stories
በማህበረሰቡ ዘንድ ይስተዋሉ የነበሩ ነባር ችግሮችን መቅረፍ የቻሉ ቴክኖሎጂዎች እያቀረበ መሆኑን የቡታጅራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አስታወቀ
ሃገሪቱ በቴክኖሎጂው ዘርፍ የያዘችውን ውጥን በማሳከቱ ረገድ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራችዎች እየተሰሩ መሆናቸው ተገለጸ
ዜጎች የተሻለ ቴክኖሎጂ ተጠቅመው ማንኛውም ተግባር እንዲያሳልጡ መንግስት ከሚሠራው በተጨማሪ የልማት አጋር አካላት ተግባር ወሳኝ መሆኑን የኣሪ ዞን አስታወቀ