አሰልጣኞች ወቅቱ የሚጠይቀውን የቴክኖሎጂ ክህሎት እንዲላበሱ እየተሠራ መሆኑ ተጠቆመ
“ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት” በሚል መሪ ቃል ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች እና ከጋምቤላ ክልሎች የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለተዉጣጡ አሰልጣኞች በቴፒ ከተማ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል።
በሥልጠናዉ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አብይ አንደሞ ፤ ይህ ስልጠና በህዳሴዉ ግብድ ምረቃ ማግስት የሚደረግ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
መንግስት ለዘርፉ በሰጠዉ ልዩ ትኩረት በትምህርትና ስልጠና ላይ በተደረገዉ ሪፎርም በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ላይ ዉጤቶች እየታዩ እንዳሉ ጠቁመዉ፤ ስልጠናው ለ693 አሰልጣኞች ለተከታታይ 12 ቀናት ይሰጣል ብለዋል፡፡
የቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ መልካሙ አየለ በበኩላቸው፤ አሰልጣኞች በየጊዜዉ ከቴክኖሎጂዉ ጋር አብረው እንዲጓዙ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ማስፈለጉን ተናግረዋል።
ሰልጣኞችም ስልጠናዉን በአግባቡ በመከታተል ተግባራዊ ሊያደርጉ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ጌትነት ገረመዉ – ከማሻ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የተለያዩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ እንደሚሠራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ
በቴክኖሎጂ የተካኑ ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት በመሥራት ሀገሪቱን ማበልጸግ እንደሚገባ ተገለጸ
በቴክኖሎጂና ፈጠራ ተወዳዳሪ የሰው ኃይል በማፍራት የኢንዱስትሪ ሽግግርን በማፋጠን የሃገር ኢኮኖሚ እንዲያድግ እየሰራ መሆኑን በስልጤ ዞን የቂልጦ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ገለፀ