በቶሮንቶ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸነፉ
በቶሮንቶ በተካሄደ የማራቶን ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸንፈዋል።
በሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1ኛ – 3ኛ በመግባት የበላይ ሆነው አጠናቀዋል።
በውድድሩ አትሌት ዋጋነሽ መካሻ 2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ 1ኛ ስትወጣ አትሌት ሮዛ ደረጀ 2ኛ እንዲሁም አትሌት አፈራ ጎድፋይ 3ኛ በመሆን አጠናቀዋል።
በሌላ በኩል በወንዶች ማራቶን አትሌት ሙሉጌታ ኡማ 2 ሰዓት ከ07 ደቂቃ ከ16 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት ውድድሩን ማሸነፍ ችሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
የሀገሪቱን ቦክስ ስፖርት ለማሳደግ የቀድሞ ቦክሰኞችና ሌሎችም አስተዋጽዋቸውን አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ ጥሪ ቀረበ
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ