በቶሮንቶ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸነፉ
በቶሮንቶ በተካሄደ የማራቶን ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸንፈዋል።
በሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1ኛ – 3ኛ በመግባት የበላይ ሆነው አጠናቀዋል።
በውድድሩ አትሌት ዋጋነሽ መካሻ 2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ 1ኛ ስትወጣ አትሌት ሮዛ ደረጀ 2ኛ እንዲሁም አትሌት አፈራ ጎድፋይ 3ኛ በመሆን አጠናቀዋል።
በሌላ በኩል በወንዶች ማራቶን አትሌት ሙሉጌታ ኡማ 2 ሰዓት ከ07 ደቂቃ ከ16 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት ውድድሩን ማሸነፍ ችሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል