በቶሮንቶ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸነፉ
በቶሮንቶ በተካሄደ የማራቶን ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸንፈዋል።
በሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1ኛ – 3ኛ በመግባት የበላይ ሆነው አጠናቀዋል።
በውድድሩ አትሌት ዋጋነሽ መካሻ 2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ 1ኛ ስትወጣ አትሌት ሮዛ ደረጀ 2ኛ እንዲሁም አትሌት አፈራ ጎድፋይ 3ኛ በመሆን አጠናቀዋል።
በሌላ በኩል በወንዶች ማራቶን አትሌት ሙሉጌታ ኡማ 2 ሰዓት ከ07 ደቂቃ ከ16 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት ውድድሩን ማሸነፍ ችሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሀዋሳ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታን አሸነፈ
ኦክስሌድ ቻምበርሌን በአርሰናል ልምምድ መስራት ጀመረ
ቱርክ 149 የእግር ኳስ ዳኞችን አገደች