በቶሮንቶ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸነፉ
በቶሮንቶ በተካሄደ የማራቶን ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸንፈዋል።
በሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ከ1ኛ – 3ኛ በመግባት የበላይ ሆነው አጠናቀዋል።
በውድድሩ አትሌት ዋጋነሽ መካሻ 2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ44 ሴኮንድ 1ኛ ስትወጣ አትሌት ሮዛ ደረጀ 2ኛ እንዲሁም አትሌት አፈራ ጎድፋይ 3ኛ በመሆን አጠናቀዋል።
በሌላ በኩል በወንዶች ማራቶን አትሌት ሙሉጌታ ኡማ 2 ሰዓት ከ07 ደቂቃ ከ16 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት ውድድሩን ማሸነፍ ችሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ
ጆሿ ዚርኪዜ በሮማ ይፈለጋል