አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝ ሆኑ
የቀድሞው የአርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝ ሆነው ተሹመዋል።
በዚህም ላለፉት 12 ወራት የብሔራዊ ቡድኑ ምክትል አሰልጣኝ የነበሩት መሳይ ተፈሪ በቀጣይ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ(ቻን) ማጣሪያ ከኤርትራ ጋር የምታከናውናቸውን ጨዋታዎች ጨምሮ የቻን ማጣሪያን በጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝ የሚመሩ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አሳውቋል።
ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር የምታደርጋቸው የደርሶ መልስ ጨዋታዎች በደቡብ ሱዳን ጁባ ብሔራዊ ስታዲየም የሚከናወኑ መሆኑን የፌዴሬሽኑ መረጃ አመላክቷል።
ጨዋታዎቹ የሚከናወኑበት ቀናትም ጥቅምት 21/2017 እና ጥቅምት 24/2017 ናቸው ተብሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
በታሪካዊው ምስል የተገናኙት ሜሲ እና ያማል፤ በዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ፊት ለፊት!
አርሰናል ክርስቶስ ዞሊስን ለማስፈረም ተስማማ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በወልቂጤ ከተማ የሰርከስ ስፖርት ምልመላና የማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት መርሃ ግብር ተካሄደ