ማንቸስተር ሲቲ በባከነ ደቂቃ በተቆጠረ ግብ ዎልቭስን አሸነፈ
በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ 8ኛ ሳምንት መርሐግብር ከሜዳው ውጪ ዎልቭስን የገጠመው ማንቸስተር ሲቲ በተጨማሪ ሰዓት በተቆጠረ ግብ ዎልቭስን 2ለ1 አሸንፏል።
በሞሊኑክስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጆስኮ ግቫርዲዮል በ33ኛው ደቂቃ እና ጆን ስቶንስ በ90+5 የማንቸስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።
ስትራንድ ላርሰን በ7ኛ ደቂቃ የዎልቭስን ጎል አስቆጥሯል።
ውጤቱን ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ በ20 ነጥብ በጊዜያዊነት የሊጉ መሪ መሆን ሲችል ዎልቭስ በ1 ነጥብ 20ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ፕሪሚዬር ሊጉ መካሄዱን ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ በአንፊልድ ሮድ ሊቨርፑል ከቼልሲ ተጠባቂ ጨዋታ የሚያከናውኑ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 አሸነፈ