ማንቸስተር ሲቲ በባከነ ደቂቃ በተቆጠረ ግብ ዎልቭስን አሸነፈ
በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ 8ኛ ሳምንት መርሐግብር ከሜዳው ውጪ ዎልቭስን የገጠመው ማንቸስተር ሲቲ በተጨማሪ ሰዓት በተቆጠረ ግብ ዎልቭስን 2ለ1 አሸንፏል።
በሞሊኑክስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጆስኮ ግቫርዲዮል በ33ኛው ደቂቃ እና ጆን ስቶንስ በ90+5 የማንቸስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።
ስትራንድ ላርሰን በ7ኛ ደቂቃ የዎልቭስን ጎል አስቆጥሯል።
ውጤቱን ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ በ20 ነጥብ በጊዜያዊነት የሊጉ መሪ መሆን ሲችል ዎልቭስ በ1 ነጥብ 20ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ፕሪሚዬር ሊጉ መካሄዱን ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ በአንፊልድ ሮድ ሊቨርፑል ከቼልሲ ተጠባቂ ጨዋታ የሚያከናውኑ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል