“ሃይማኖቶች ለሰላም፣ ለመከባበር እና ለአንድነት” በሚል መሪ ቃል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃይማኖት ተቋማት ከክልሉ መንግስት ጋር በመተባበር በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ ብፁዕ አቡነ ህርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ፓትርያርኩና የኢሃተጉ የበላይ ጠባቂ ተወካይ፣ ክቡር ሽይኽ አብዱልከሪም ሽይኽ በድረዲን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንትና የኢሃተጉ የበላይ ጠባቂ ተወካይ፣ ክቡር ቄስ ደረጀ ጀምበሩ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንትና የኢሃተጉ የበላይ ጠባቂ ተወካይ፣ ብፁዕ አቡነ ስዩም ፍራንሷ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የብፁዕ ካርዲናልና የኢሃተጉ የበላይ ጠባቂ ተወካይ፣ ፓስተር ታደሠ አዱኛ የኢትዮጵያ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ፕሬዝዳንትና የኢሃተጉ የበላይ ጠባቂ ተወካይ እንዲሁም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር እና የዕለቱ የክብር እንግዳ እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ጨምሮ የሃይማኖት መሪዎች የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ሀድያ ዞን እና የሆሣዕና ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች የሁሉም ቤተ-እምነት ተከታዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በአሁኑ ሰዓት በየሃይማኖቱ ወጣት መዘምራን መንፈሳዊ መዝሙሮች እየቀረቡ ይገኛል፡፡
ዘጋቢ፡ በየነ ሰላሙ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ
የአብሮነት ምልዕክት
የቡታጅራ ግራንድ ቪው ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን 164 ተማሪዎች ለ2ኛ ዙር አስመረቀ