አርባምንጭ ከተማ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚዬርሊግ መመለሱን አረጋገጠ
በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ለ ተሳታፊ የሆነው አርባምንጭ ከተማ ቀሪ 3 ጨዋታዎች እያሉት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚዬርሊግ ማደጉን አረጋግጧል።
አርባምንጭ ከተማ ወደ ፕሪሚዬር ሊጉ ማደጉን ያረጋገጠው በዛሬው ዕለት በ23ኛ ሳምንት ቦዲቲ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፎ ነው።
ክለቡ በ2015 የውድድር ዘመን ከፕሪሚዬርሊጉ ወደ ከፍተኛ ሊጉ የወረደ ሲሆን በወረደበት ዓመት ወደ ሃገሪቱ ቀዳሚው የሊግ እርከን መመለስ ችሏል
አዘጋጅ ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
የሀገሪቱን ቦክስ ስፖርት ለማሳደግ የቀድሞ ቦክሰኞችና ሌሎችም አስተዋጽዋቸውን አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ ጥሪ ቀረበ
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ