አርባምንጭ ከተማ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚዬርሊግ መመለሱን አረጋገጠ

አርባምንጭ ከተማ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚዬርሊግ መመለሱን አረጋገጠ

በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ለ ተሳታፊ የሆነው አርባምንጭ ከተማ ቀሪ 3 ጨዋታዎች እያሉት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚዬርሊግ ማደጉን አረጋግጧል።

አርባምንጭ ከተማ ወደ ፕሪሚዬር ሊጉ ማደጉን ያረጋገጠው በዛሬው ዕለት በ23ኛ ሳምንት ቦዲቲ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፎ ነው።

ክለቡ በ2015 የውድድር ዘመን ከፕሪሚዬርሊጉ ወደ ከፍተኛ ሊጉ የወረደ ሲሆን በወረደበት ዓመት ወደ ሃገሪቱ ቀዳሚው የሊግ እርከን መመለስ ችሏል

አዘጋጅ ፡ ሙሉቀን ባሳ