ኮሌጁ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮ የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያተኮረ ስልጠና እየሰጠ ነው።
የኮሌጁ ዲን አቶ አንዱዓለም ገብረመድህን በመክፈቻ ንግግራቸው፤ የወጣቶችን ስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
ኮሌጁ ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት በተለያዩ ዘርፎች ለበርካታ ዜጎች ለስራ ፈጠራ አጋዥ የሚሆኑ ስልጠናዎችን እየሰጠ ነው ብለዋል።
ኮሌጁ በርካታ የስልጠና አማራጮች ያሉት በመሆኑ ዜጎች ወደ ኮሌጁ በመምጣት የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከማሰልጠን ባሻገር ለወጣቱ ስራ ዕድል መፍጠር የኮሌጁ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኮሌጁ ምክትል ዲን ወይዘሮ ለጢፋ አህመድ ናቸው።
እየተሰጠ ያለው ስልጠና በስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የሚታዩ ክፍተቶችን በመሙላት ዘላቂ የሆነ የወጣቶች ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።
ስልጠናው ለተከታታይ 21 ቀናት የሚሰጥ መሆኑን ተናግረው፤ ሰልጣኞች በአግባቡ ተከታትለው ተጠቃሚ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮ የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት አስተባባሪ አሸብር ቆጭቶ(ዶ/ር)፤ ስልጠናው ወጣቶችን ከስራ ጋር ለማስተሳሰር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አመላክተዋል።
ከካፋና ከምዕራብ ኦሞ ዞኖች ቆላማ አካባቢዎች የተውጣጡ በማህበር የተደራጁ ወጣቶች በዳቦ መጋገሪያና በእንጨት ስራዎች ዙሪያ ስልጠና መጀመራቸውን ገልጸዋል።
ሰልጣኞች በተደራጁበት ስራ የጽንሰ ሀሳብ ስልጠና ከተሰጣቸው በኋላ የተግባር ልምምድ እንደሚያደርጉ አመላክተዋል።
ዘጋቢ፡ ሀብታሙ ኃይሌ – ከቦንጋ ጣቢያችን
የወጣቶችን ስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን የቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ገለጸ
ኮሌጁ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮ የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያተኮረ ስልጠና እየሰጠ ነው።
የኮሌጁ ዲን አቶ አንዱዓለም ገብረመድህን በመክፈቻ ንግግራቸው፤ የወጣቶችን ስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ የተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
ኮሌጁ ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት በተለያዩ ዘርፎች ለበርካታ ዜጎች ለስራ ፈጠራ አጋዥ የሚሆኑ ስልጠናዎችን እየሰጠ ነው ብለዋል።
ኮሌጁ በርካታ የስልጠና አማራጮች ያሉት በመሆኑ ዜጎች ወደ ኮሌጁ በመምጣት የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከማሰልጠን ባሻገር ለወጣቱ ስራ ዕድል መፍጠር የኮሌጁ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የኮሌጁ ምክትል ዲን ወይዘሮ ለጢፋ አህመድ ናቸው።
እየተሰጠ ያለው ስልጠና በስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የሚታዩ ክፍተቶችን በመሙላት ዘላቂ የሆነ የወጣቶች ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።
ስልጠናው ለተከታታይ 21 ቀናት የሚሰጥ መሆኑን ተናግረው፤ ሰልጣኞች በአግባቡ ተከታትለው ተጠቃሚ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮ የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት አስተባባሪ አሸብር ቆጭቶ(ዶ/ር)፤ ስልጠናው ወጣቶችን ከስራ ጋር ለማስተሳሰር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አመላክተዋል።
ከካፋና ከምዕራብ ኦሞ ዞኖች ቆላማ አካባቢዎች የተውጣጡ በማህበር የተደራጁ ወጣቶች በዳቦ መጋገሪያና በእንጨት ስራዎች ዙሪያ ስልጠና መጀመራቸውን ገልጸዋል።
ሰልጣኞች በተደራጁበት ስራ የጽንሰ ሀሳብ ስልጠና ከተሰጣቸው በኋላ የተግባር ልምምድ እንደሚያደርጉ አመላክተዋል።
ዘጋቢ፡ ሀብታሙ ኃይሌ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ
የአብሮነት ምልዕክት
የቡታጅራ ግራንድ ቪው ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን 164 ተማሪዎች ለ2ኛ ዙር አስመረቀ