ሀዋሳ፡ ነሐሴ 28/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የዘመን መለወጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ አንዳንድ ነጋዴዎችና ተቋማት ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዳያደርጉ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቅድመ ዝግጅት ሥራ ማጠናቀቁን የኮንታ ዞን ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
እንደ ሀገር የተፈጠረውን የኑሮ ውድነት ተከትሎ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ለመከላከልና ለመቆጣጠር ዝግጅት መጠናቀቁን የዞኑ ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ንጋቱ ኬሃሞ ተናግረዋል።
ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዲባባስ የሚያደርጉ ደላላዎችን ከገበያ የማውጣት ስራ እየተሠራ መሆኑን አቶ ንጋቱ ገልፀዋል።
በዓልን ምክንያት በማድረግ አላስፈላጊ የሆነ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎችም ሆነ ድርጅቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስዱም ጭምር ነው ኃላፊው አክለው ያሳሰቡት።
በዞኑ አመያ ከተማ ገበያ ለበዓል ሰንጋ ሲገዙ ካገኘናቸው መካከል አቶ ታጋይ ዶኖቾና ሌሎችም በሰጡን ሀሳብ የበዓል ገበያ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ማሳየቱን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ደረጀ ተፈራ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በሀገሪቱ የሚገኙ ውሃ አዘል መሬቶችንና ተፋሰሶችን የማልማት ተግባር በጥናት በማስደገፍ እየተከናወነ መሆኑ ተገለጸ
ከ16 ሺህ 800 ሄክታር በላይ መሬት በበልግ እርሻ በበቆሎ ማሳ ለመሸፈን እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
“የተፈጥሮ ሀብት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ሊሰራ ይገባል” – የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት