ሀዋሳ፡ ነሐሴ 28/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የዘመን መለወጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ አንዳንድ ነጋዴዎችና ተቋማት ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዳያደርጉ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቅድመ ዝግጅት ሥራ ማጠናቀቁን የኮንታ ዞን ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
እንደ ሀገር የተፈጠረውን የኑሮ ውድነት ተከትሎ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ለመከላከልና ለመቆጣጠር ዝግጅት መጠናቀቁን የዞኑ ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ንጋቱ ኬሃሞ ተናግረዋል።
ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ እንዲባባስ የሚያደርጉ ደላላዎችን ከገበያ የማውጣት ስራ እየተሠራ መሆኑን አቶ ንጋቱ ገልፀዋል።
በዓልን ምክንያት በማድረግ አላስፈላጊ የሆነ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎችም ሆነ ድርጅቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስዱም ጭምር ነው ኃላፊው አክለው ያሳሰቡት።
በዞኑ አመያ ከተማ ገበያ ለበዓል ሰንጋ ሲገዙ ካገኘናቸው መካከል አቶ ታጋይ ዶኖቾና ሌሎችም በሰጡን ሀሳብ የበዓል ገበያ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ማሳየቱን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ደረጀ ተፈራ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ በመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሰኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አሰታወቀ
ሳውላ ከተማን ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ምቹ የማድረግ የ5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተካሄደ ነው
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቱሪዝም ሀብቶችን በማልማትና ሰላምን በማጽናት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል