ሀዋሳ: ግንቦት 24/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓመተ-ምህረት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በካፋ ዞን ከሚገኙ የምርጫ ክልሎች ውስጥ አንዱ በሆነው በቢጣ ጌሻ ምርጫ ክልል ዜጎች ሌሊት 11:30 ጀምረው ከቤታቸው በመውጣት በድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ተገኝተዋል፡፡
ተንቀሳቅሰን የተመለከትናቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የተለያዩ የምርጫ ታዛቢዎች ተሟልተው መገኘታቸውን ማረጋገጥ ተችሏል፡፡
አስፈላጊ የፀጥታ አካላትም በምርጫ ጣቢያዎቹ የጽጥታ ሥራዎችን ለማገዝ በስፍራው ተገኝተዋል፡፡
በዚህም በየምርጫ ጣቢያዎቹ የተገኙ ዜጎች ይበጀናል ለሚሉት የፖለቲካ ፓርቲ ድምፃቸውን መስጠት ጀምረዋል፡፡
የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ የጀመረ ሲሆን የዜጎች ተሳትፎም ከወዲሁ ንቁ መሆኑን መገንዘብ ተችሏል፡፡
ዘጋቢ ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ በ2018 በጀት አመት ከ336 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ከምዝበራና ከብክነት ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ45.7 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አፀደቀ
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት