‎ለተከታታይ 7 ምርጫዎች የተሳተፉ የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች



‎ኢትዮጵያ በዛሬዉ ዕለት እያካሄደች የሚገኘውን 7ኛ ጠቅላላ ምርጫን ጨምሮ ሁሉንም ምርጫዎች መሳተፋቸውን የጃጁራ ከተማ  አስተዳደር ነዋሪ የሆኑት፥ አቶ ዳንኤል ሌረሞ እና አቶ ዳየሞ ጡሜቦ ይገልፃሉ።



‎ነዋሪዎቹ እንደሚሉት፤ አንድ ድምፅ ለአሸናፊነት አልያም ለተሸናፊነት ሊያበቃ እንደሚችል ያላቸዉ ግንዛቤ በቀደሙት ምርጫዎችና በዘንድሮውም ጭምር እንዲሳተፉ አድርጓቸዋል።



‎ከእስከዛሬው ምርጫ በተለየ በርካቶች ወጥተዉ እየመረጡ መሆናቸው የዘንድሮዉ 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ለየት እንደሚያደርገውና በሰላምና ጤና ተገኝተዉ መሳተፍ በመቻላቸዉ የፈጠረባቸዉን ልዩ ስሜት ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ገልፀዋል።



‎በዚህም የመረጡት ፓርቲ አሸንፎ እንድትሆን የሚመኟት የወደፊቷን ኢትዮጵያ ለማስቀጠል የበኩላቸዉን ለመወጣት ስለዝግጁነትና ተስፋቸው ይናገራሉ።



‎የራስን እድል በራስ መወሰን ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን ጠቁመዉ፤ ምርጫውን ነፃና ፍትሐዊ ሆኖ እንዳገኙትም አክለዋል።



‎ዘጋቢ ፡ ብዙነሽ ዘዉዱ