ኢትዮጵያ በዛሬዉ ዕለት እያካሄደች የሚገኘውን 7ኛ ጠቅላላ ምርጫን ጨምሮ ሁሉንም ምርጫዎች መሳተፋቸውን የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪ የሆኑት፥ አቶ ዳንኤል ሌረሞ እና አቶ ዳየሞ ጡሜቦ ይገልፃሉ።
ነዋሪዎቹ እንደሚሉት፤ አንድ ድምፅ ለአሸናፊነት አልያም ለተሸናፊነት ሊያበቃ እንደሚችል ያላቸዉ ግንዛቤ በቀደሙት ምርጫዎችና በዘንድሮውም ጭምር እንዲሳተፉ አድርጓቸዋል።
ከእስከዛሬው ምርጫ በተለየ በርካቶች ወጥተዉ እየመረጡ መሆናቸው የዘንድሮዉ 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ለየት እንደሚያደርገውና በሰላምና ጤና ተገኝተዉ መሳተፍ በመቻላቸዉ የፈጠረባቸዉን ልዩ ስሜት ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ገልፀዋል።
በዚህም የመረጡት ፓርቲ አሸንፎ እንድትሆን የሚመኟት የወደፊቷን ኢትዮጵያ ለማስቀጠል የበኩላቸዉን ለመወጣት ስለዝግጁነትና ተስፋቸው ይናገራሉ።
የራስን እድል በራስ መወሰን ትልቅ አጋጣሚ መሆኑን ጠቁመዉ፤ ምርጫውን ነፃና ፍትሐዊ ሆኖ እንዳገኙትም አክለዋል።
ዘጋቢ ፡ ብዙነሽ ዘዉዱ

More Stories
በክልሉ በ2018 በጀት አመት ከ336 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ከምዝበራና ከብክነት ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ45.7 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አፀደቀ
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት