በመሎ ኮዛ ምርጫ ክልል በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምፅ መስጠት ተጀመረ



‎በመሎ ኮዛ ምርጫ ክልል በላሃ ከተማ በላሃ ከተማ ቦክሬ ማዞሪያ ምርጫ ጣቢያ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን እንደ ተመላከተው ከማለዳ 12:00 ሰዓት የምርጫ አስፈፃሚዎችና ወኪል ታዛቢዎች በተገኙበት የድምፅ መስጫ ሳጥን ባዶ መሆኑና ሌሎች ቁሳቁሶች መሟላታቸው ተረጋግጦ የድምፅ መስጠት መርሀ-ግብሩ በይፋ ተጀምሯል።

‎የመራጭነት ካርድ የወሰዱ ዜጎች  ከሌሊቱ 12፡00 ሰዓት አስቀድሞ ሰልፍ በመያዝ ድምጽ እየሰጡ ይገኛል፡፡

‎በቀዳሚነት ድምፅ ከሰጡት የመሎ ኮዛ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሉነህ አውሳተው ከምርጫ በኋላ በሰጡት ሀሳብ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዲሞክራሲ ስርዓትን መሰረት የምናስይዝበት ነው ብለዋል።

‎በወረዳው የብልጽግና፣ ኢዜማ ፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት፣ነፃነትና ዕኩልነት፣ ኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ኅብር ፓርቲዎች ይፎካከራሉ።

‎ዘጋቢ፡ ድጋፌ ድክሬ – ከሳውላ ጣቢያችን