በመሎ ኮዛ ምርጫ ክልል በላሃ ከተማ በላሃ ከተማ ቦክሬ ማዞሪያ ምርጫ ጣቢያ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን እንደ ተመላከተው ከማለዳ 12:00 ሰዓት የምርጫ አስፈፃሚዎችና ወኪል ታዛቢዎች በተገኙበት የድምፅ መስጫ ሳጥን ባዶ መሆኑና ሌሎች ቁሳቁሶች መሟላታቸው ተረጋግጦ የድምፅ መስጠት መርሀ-ግብሩ በይፋ ተጀምሯል።
የመራጭነት ካርድ የወሰዱ ዜጎች ከሌሊቱ 12፡00 ሰዓት አስቀድሞ ሰልፍ በመያዝ ድምጽ እየሰጡ ይገኛል፡፡
በቀዳሚነት ድምፅ ከሰጡት የመሎ ኮዛ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሉነህ አውሳተው ከምርጫ በኋላ በሰጡት ሀሳብ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዲሞክራሲ ስርዓትን መሰረት የምናስይዝበት ነው ብለዋል።
በወረዳው የብልጽግና፣ ኢዜማ ፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት፣ነፃነትና ዕኩልነት፣ ኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ኅብር ፓርቲዎች ይፎካከራሉ።
ዘጋቢ፡ ድጋፌ ድክሬ – ከሳውላ ጣቢያችን
በመሎ ኮዛ ምርጫ ክልል በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምፅ መስጠት ተጀመረ

More Stories
በካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ሞርጫ ክልል መራጮች ድምጽ መስጠት ጀምረዋል፡፡
ለተከታታይ 7 ምርጫዎች የተሳተፉ የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች
የሀገሪቱ የነገ “ዕጣ ፈንታ” የሚወሰነው በምርጫ ነው – የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች