ከ107 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ18 ነጥብ 7 ኪ.ሜ አዲስ የመንገድ ግንባታ ተጀመረ

ከ107 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ18 ነጥብ 7 ኪ.ሜ አዲስ የመንገድ ግንባታ ተጀመረ

ሀዋሳ፡ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ በጎፋ ዞን መሎኮዛ ወረዳ ከ107 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ18 ነጥብ 7 ኪ.ሜ አዲስ የመንገድ ግንባታ አስጀመረ።

‎በጎፋ ዞን መሎኮዛ ወረዳ የሚስተዋለውን የመንገድ ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል።

‎የመሎ ኮዛ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሉነህ አውሳቶ ህብረተሰቡ የረዥም ዘመናት ጥያቄ ሆኖ የቆየው የመንገድ ግንባታ ሥራው በተቆረጠለት ጊዜ በፈጥነት ተጠናቆ ለሕዝብ አገልግሎት እንዲደርስ እንዲደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

‎የጎፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ስራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ምናሴ ኤሊያስ፤ የመንገዱ መጀመር በወረዳው ምርትና ምርታማነትን በመጨመር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማረጋገጥና የገበያ ትሰሰር እንደሚያሳልጥ ተናግረዋል።

‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወልደ ተሰፋዬ የመንገዱ ስራ በገጠር ትስስርና በምግብ ዋስትና ፕሮግራም አማካኝነት የሚሰራ መሆኑ ተናግረዋል።

በ107 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር 18.7 ኪ.ሜ የሚሰራው ከወረዳ ከዞን እስከ ክልል ያሉ የመንግስት ተቋማት በማቺንግ ፈንድ የሚተገበር ሲሆን 70% በአለም ባንክ ድጋፍ የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የ‎መንገዱ ስራ በቀጣይ አራት ወራት የሚጠናቀቅ ሲሆን ከወረዳ እስከ ክልል ያሉ የመንግስት አካላት ድጋፍና የቅርብ ክትትል የሚደረግ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎ዘጋቢ፡ ስንታየሁ ሙላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን