ማንቸስተር ዩናይትድ አንድሬ ሳንቶስን አስፈረመ
ማንቸስተር ዩናይትድ አንድሬ ሳንቶስን ከቼልሲ በይፋ አስፈርሟል።
ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹን በ50 ሚልዮን ፓውንድ ሲያስፈርም ቼልሲ ከወደፊት ሽያጩ 10 በመቶ ድርሻ የሚያገኝ ይሆናል።
በዚህ ክረምት ለቀያይ ሰይጣኖች የመጀሪያው ፈራሚ የሆነው የ22 ዓመቱ አንድሬ ሳንቶስ ከማንቸስተር ዩናይትድ ጋር ተጨማሪ 12 ወራትን ያካተተ የ5 ዓመት ኮንትራት መፈራረሙ ተገልጿል።
በዝውውር መስኮቱ በዋነኝነት የአማካይ ክፍሉን ለማጠናከር እንቅሰቃሴ በማድረግ ላይ የሚገኘው ማንቸስተር ዩናይትድ ቤልጂዬማዊውን አማካይ ዩሪ ቴሊማንስን ከአስቶንቪላ ለማስፈረም ከስምምነት ላይ መድረሱ ታውቋል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የ2018 የCBE የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን በማሸነፍ ሁለት ዋንጫ ላነሳው የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ክልሉ ያዘጋጀውን የዕውቅናና የሽልማት ፕሮግራም ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 06/2018 ከቀኑ 12፡00 ጀምሮ በሀዋሳ ሀይሌ ሪዞርት ይካሄዳል።
አሌሃንድሮ ጋርናቾ ከቼልሲ ጋር ያለው የወደፊት ዕጣ ፈንታ በአጣብቂኝ ውስጥ
አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ በሪያል ማድሪድ ስራቸውን ጀመሩ