ማሳቸውን ለመኸር እርሻ ደጋግማው በማረስ አለስልሰው በወቅቱ ለመዝራት መዘጋጀታቸውን በከምባታ ዞን ቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ያነጋገርናቸው አንዳንድ አርሶአደሮች ተናገሩ
ለ2018/19 ዓ ም ምርት ዘመን በመኸር እርሻ 2 ሺ 9 መቶ 12 ሄክታር ማሳ በዘር ለመሸፈን አቅዶ እየሰራ መሆኑን በከምባታ ዞን የቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስታዉቋል።
ያላቸውን ማሳ በዘር ለመሸፈን የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን አጠናቀው ወቅቱን በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን የቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ አርሶአደሮች አስረድተዋል።
ከተለመደው አስተራረስ ዘዴ በመላቀቅ ስንዴና ጤፍን በኩታ ገጠም በክላስተር ለመዝራት የሚያስችል የማሳ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
መንግስት የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እና ዋጋው የአርሶ አደሩን አቅም ባገናዘበ መልኩ እንዲሆን መስራት እንዳለበት አርሶአደሮቹ ጠይቀዋል።
“የተቀናጀ ግብርና ትጋት ለላቀ ምርታማነት” በሚል መሪ ቃል የ2018 የምርት ዘመን የመኸር ወቅት የተቀናጀ ግብርና ልማት ሥራዎችን በንቅናቄ መምራት በሚያስችል ሁኔታ ላይ አርሶ አደሮችን፣ የግብርና ባለሙያዎችንና የሚመለከታቸውን በማሳተፍ የዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት የቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳዊት ማቴዎስ ናቸው።
በ2018/19 ምርት ዘመን 2 ሺ 912.5 ሄክታር ማሳ በዘር ለመሸፈን የሚያስችል የማሳ ዝግጅትና የግብዓት አቅርቦት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አስረድተዋል።
አርሶ አደሩ ዘመናዊ አስተራረስ ዘዴዎችን እንዲከተል ለማስቻል እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ዳዊት፤ በክላስተር በኩታ ገጠም መዝራት ከአረም ቁጥጥር ባሻገር ምርትና ምርተማነትን ለማሳደግ ምቹ ሁኔተን ይፈጥራል ነው ያሉት።
29 የስንዴ እና 26 የጤፍ ክላስተር ተለይቶ መዘጋጀቱን የጠቆሙት ኃላፊው፤ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ላይ ከወትሮ የተለየ የዋጋ ለውጥ እንዳይኖር መሠራቱን አመላክተዋል።
ዘጋቢ: አለማየሁ ማተቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ የስራ ዘርፎች ከ40 ሺህ በላይ ወጣቶችን ተሳታፊ በማድረግ 46 ሚሊዮን 620 ሺህ ብር በላይ ከመንግሥት ሊወጣ የሚችለውን ለማዳን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አስታወቀ
የቀቤና ልዩ ወረዳ ማህበረሰብ የልማት ፍላጎት ማሟላት የሚቻለው ግብርና ታክስ በታማኝነትና በወቅቱ መክፈል ሲቻል መሆኑ ተገለጸ
በ2018 ከደረጃ “ለ” ከ13 ሺህ 300 ግብር ከፋዮች ከ80 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል – በሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት