ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አስፈረመ

ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አስፈረመ

ማንቸስተር ዩናይትድ ከሊድስ ዩናይትድ ጋር የተለያየውን ግብ ጠባቂ ካርል ዳርሎውን በነፃ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል።

ዌልሳዊው ግብ ጠባቂ ካርል ዳርሎው በዩናይትድ እስከ 2028 ድረስ የሚያቆየውን የሁለት ዓመት ኮንትራት ተፈራርሟል።

በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ላይ ማንቸስተር ዩናይትድ አንድሬ ሳንቶስን ከቼልሲ ያስፈረመ ሲሆን፤ ዩሪ ቴሊማንስንም ከአስቶንቪላ ለማስፈረም ከስምምነት ላይ መድረሱ ይታወቃል።

ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ