ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው የጂንካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት የተጠርጣሪ ማቆያና የቢሮ ህንጻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው በተገኙበት በደማቅ ሥነ ስርዓት በይፋ ተመረቀ
በማህበረሰብ ተሳትፎ በተገነባው ህንጻ ምረቃ ላይ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ከፍተኛ የጸጥታ ዘርፍ አመራሮች ተገኝተዋል።
በህዝብ ተሳትፎ የተገነባው የጂንካ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ለዓመታት ሲያገለግል የቆየውን የፖሊስ ተቋም በአዲስ መልክ መቀየር ያስችላል ተብሏል።
ከ21 ሚሉዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው ህንጻ በልዩ የባዛር ዝግጅት በድምቀት የመረቁት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው በጋራ በመሆን ነው።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የጸጥታ አመራሮች በልዩ የባዛር ዝግጅት ላይ በክብር እንግድነት ታድመዋል።
ለ3 ቀናት በሚቀጥለው የባዛር ዝግጅት ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማግኘት የታቀደ ሲሆን ይህም የተቋሙን የውስጥ ግብዓት ለማሟላት በማለም የተሰናዳ መሆኑን ከአስመራቂ ኮሚቴ አመራሮች መረዳት ተችሏል።
ዘጋቢ፡ ወንድሜነህ አድማሱ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ማሳቸውን ለመኸር እርሻ ደጋግማው በማረስ አለስልሰው በወቅቱ ለመዝራት መዘጋጀታቸውን በከምባታ ዞን ቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ያነጋገርናቸው አንዳንድ አርሶአደሮች ተናገሩ
በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ የስራ ዘርፎች ከ40 ሺህ በላይ ወጣቶችን ተሳታፊ በማድረግ 46 ሚሊዮን 620 ሺህ ብር በላይ ከመንግሥት ሊወጣ የሚችለውን ለማዳን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አስታወቀ
የቀቤና ልዩ ወረዳ ማህበረሰብ የልማት ፍላጎት ማሟላት የሚቻለው ግብርና ታክስ በታማኝነትና በወቅቱ መክፈል ሲቻል መሆኑ ተገለጸ