የዳውሮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ ሥራ ዘመን 29ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባዔ አቶ ዳዊት ሚኖታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በታሪኳ በሃሳብ ልዕልና ላይ ለመመሥረት ሀገራዊ ምክክር እያካሄደች ባለችበት ወቅት መካሄዱ ጉባዔውን ልዩ ያደርገዋል።
ምክር ቤቶች የዲሞክራሲ ተቋማትና የህዝብ ሉዓላዊነት መገለጫ መሆናቸውን ያመለከቱት ዋና አፈ ጉባዔው፤ ተቋማቱ ቀጥተኛ የህዝብ ውክልና የሚንጸባረቅባቸው መድረኮች መሆናቸውን አብራርተዋል።
ምክር ቤቱ በቆይታው፤ የዞኑን ምክር ቤት፣ የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን እና የዞኑን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ላይ ተወያይቶ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የ2019 የበጀት ረቂቅ እና የእሰራ ባሌ ከተማ አስተዳደር አዲስ የቀበሌ መዋቅር ቀርበው እንደሚጸድቁም ተመላክቷል፡፡
ዘጋቢ፡ እሸቱ ወርቅነህ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የትምህርት ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ግምገማ እና የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ቅበላ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው
የህግ ታራሚዎችን አምራች ዜጋ ለማድረግ የስነ-ልቦና ድጋፍና የክህሎት ማጎልበቻ ስራዎች ወሳኝ መሆናቸው ተገለጸ
የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ አመት የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል