ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ኢሠራ ወረዳ የተሠራውን 40 ኪሎ ሜትር መንገድ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 22/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ኢሠራ ወረዳ የተሠራውን ከሰንገጢ – ጩርጩራ 40 ኪሎ ሜትር መንገድ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
በመንገዱ ግንባታ 2 ድልድዮች የተካተቱ ሲሆን አጠቃላይ በአንድ መቶ አስራ ስምንት ሚሊየን ብር ወጪ የተሠራ ፕሮጀክት መሆኑ ተገልጿል።
5 ቀበሌያትን አቋርጦ የሚያልፈው ይህ መንገድ በገጠር መንገድ ታርጫ ዲስትሪክት የተሠራ መሆኑም ተጠቁሟል።
መንገዱ የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ ሲሆን አቋርጦ የሚያልፍባቸው አካባቢዎችም በርካታ የግብርና ምርቶች ያሉበት እንደሆነ ተመላክቷል።
አርሶ አደሮች በአካባቢው ያሉ የግብርና ምርቶችን ለማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ የመንገዱ ግንባታ ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለው ተጠቅሷል።
በመርሃ-ግብሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ መሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የመንገድና ትራንስፖርት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒን ጨምሮ ከፍተኛ የክልልና የዞን አመራሮች እንዲሁም የአካባቢ ማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የብራይት ፕሮጀክት የሴቶችንና ህፃናትን የስራ ጫና ከማቃለል ባሻገር የንፁህ መጠጥ ውሀ ተደራሽነት ላይ የሚመታይ ተግባር ማከናወኑን የጋሞ ዞን ውሀና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጥናታቸው በተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች ላይ ያተኮረ የማረጋገጫ ወርክሾፕ እና የርክክብ መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል
የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት የቤት ልማት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ