ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ኢሠራ ወረዳ የተሠራውን 40 ኪሎ ሜትር መንገድ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 22/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ኢሠራ ወረዳ የተሠራውን ከሰንገጢ – ጩርጩራ 40 ኪሎ ሜትር መንገድ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
በመንገዱ ግንባታ 2 ድልድዮች የተካተቱ ሲሆን አጠቃላይ በአንድ መቶ አስራ ስምንት ሚሊየን ብር ወጪ የተሠራ ፕሮጀክት መሆኑ ተገልጿል።
5 ቀበሌያትን አቋርጦ የሚያልፈው ይህ መንገድ በገጠር መንገድ ታርጫ ዲስትሪክት የተሠራ መሆኑም ተጠቁሟል።
መንገዱ የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ ሲሆን አቋርጦ የሚያልፍባቸው አካባቢዎችም በርካታ የግብርና ምርቶች ያሉበት እንደሆነ ተመላክቷል።
አርሶ አደሮች በአካባቢው ያሉ የግብርና ምርቶችን ለማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ የመንገዱ ግንባታ ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለው ተጠቅሷል።
በመርሃ-ግብሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ መሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የመንገድና ትራንስፖርት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒን ጨምሮ ከፍተኛ የክልልና የዞን አመራሮች እንዲሁም የአካባቢ ማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ባሌ ከተማ አስተዳደር ሶዶ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን መርቀው ከፈቱ
በከተማ ያለውን ህገወጥ የንግድ ስርዓት እና ኮንትሮባንድን በማስቀረት ህጋዊ ነጋዴዎችን የመደገፍ እና የማበረታታት ስራ እንደሚሰራ ተገለጸ
የግብርና ምርት ላይ የሚደረጉ ህገወጥ የዋጋ ጭማሪዎችን ለመከላከልና ለማረም ሸማቾች ከመንግስት ጋር በቅንጅት ሊስራ እንደሚገባ ተገለጸ