ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ኢሠራ ወረዳ የተሠራውን 40 ኪሎ ሜትር መንገድ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 22/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በዳውሮ ዞን ኢሠራ ወረዳ የተሠራውን ከሰንገጢ – ጩርጩራ 40 ኪሎ ሜትር መንገድ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
በመንገዱ ግንባታ 2 ድልድዮች የተካተቱ ሲሆን አጠቃላይ በአንድ መቶ አስራ ስምንት ሚሊየን ብር ወጪ የተሠራ ፕሮጀክት መሆኑ ተገልጿል።
5 ቀበሌያትን አቋርጦ የሚያልፈው ይህ መንገድ በገጠር መንገድ ታርጫ ዲስትሪክት የተሠራ መሆኑም ተጠቁሟል።
መንገዱ የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ ሲሆን አቋርጦ የሚያልፍባቸው አካባቢዎችም በርካታ የግብርና ምርቶች ያሉበት እንደሆነ ተመላክቷል።
አርሶ አደሮች በአካባቢው ያሉ የግብርና ምርቶችን ለማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ የመንገዱ ግንባታ ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለው ተጠቅሷል።
በመርሃ-ግብሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ መሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የመንገድና ትራንስፖርት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒን ጨምሮ ከፍተኛ የክልልና የዞን አመራሮች እንዲሁም የአካባቢ ማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተመራ የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲና የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች ቡድን በሰሜን ኣሪ ወረዳ በመገኘት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ተግባራትን መረቀ
ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው የጂንካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት የተጠርጣሪ ማቆያና የቢሮ ህንጻ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው በተገኙበት በደማቅ ሥነ ስርዓት በይፋ ተመረቀ
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ1 ቢሊዮን 4 መቶ 21 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የጎፋ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ