ባንኩ አዳዲስ የዲጂታል አገልግሎቶች መጀመሩን አስታወቀ

ባንኩ አዳዲስ የዲጂታል አገልግሎቶች መጀመሩን አስታወቀ

አዳዲስ ዲጂታል አገልግሎቶችን ማቅረቡን የዳሽን ባንክ አስታውቋል፡፡

ባንኩ ከዓለም አቀፍ የባንክ ተቋማት ጋር በመተባበርም የተለያዩ ዓለም አቀፍ ክፍያዎችን መክፈል የሚያስችል አገልግሎት መስጠት መጀመሩንም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው የማስተዋወቂያ መርሐ-ግብር ላይ ተገልጿል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ኘሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ አዳቶ፣ የተማሪዎች አገልግሎት ዲን አማሎ ሶጋ(ዶ/ር)፣ የሀዋሳ ዳሽን ባንክ ዲስትሪክት ጽ/ቤት ቢዝነስ ዳይሬክተር አቶ አስናቀ ደምሴ፣ የዳሽን ባንክ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆች እንዲሁም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ካውንስል እና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተገኝተዋል፡፡

ዘጋቢ፡ መዝሙረ ዳዊት