ባንኩ አዳዲስ የዲጂታል አገልግሎቶች መጀመሩን አስታወቀ
አዳዲስ ዲጂታል አገልግሎቶችን ማቅረቡን የዳሽን ባንክ አስታውቋል፡፡
ባንኩ ከዓለም አቀፍ የባንክ ተቋማት ጋር በመተባበርም የተለያዩ ዓለም አቀፍ ክፍያዎችን መክፈል የሚያስችል አገልግሎት መስጠት መጀመሩንም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው የማስተዋወቂያ መርሐ-ግብር ላይ ተገልጿል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ኘሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ አዳቶ፣ የተማሪዎች አገልግሎት ዲን አማሎ ሶጋ(ዶ/ር)፣ የሀዋሳ ዳሽን ባንክ ዲስትሪክት ጽ/ቤት ቢዝነስ ዳይሬክተር አቶ አስናቀ ደምሴ፣ የዳሽን ባንክ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆች እንዲሁም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ካውንስል እና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ መዝሙረ ዳዊት

More Stories
ምክር ቤቱ በ2018 በጀት አመት ሪፖርት እና የ2019 ጠቋሚ እቅድ ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምጽ አጸደቀ
በበጀት አመቱ ከ26 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
በበጀት ዓመቱ ከ379 ሺ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)