በክልሉ ከቱሪዝሙ ዘርፍ ባለፉት 9 ወራት 925.6 ሚሊዮን ብር ተገኝቷል
ባለፉት 9 ወራት 925.6 ሚሊዮን ብር መገኘቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለፀ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊው አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ በሰጡት መግለጫ በበጀት ዓመቱ 33 ሺ 800 የውጭ ሀገር ቱሪስቶች ክልሉን ጎብኝተው 364 ሚሊዮን ብር ገቢ መገኘቱ ገልፀዋል፡፡
በአጠቃላይ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር ቱሪሰቶች ባለፉት 9 ወራት 925.6 ሚሊዮን ብር መገኘቱንም ኃላፊው አብራርተዋል።
ክልሉ ያለው ሰው ሰራሽ፣ ተፈጥሯዊና ባህላዊ አቅሞች ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ እንዲሆን እንዳደረገው ገልፀዋል፡፡
የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ አሁን ላይ ለመሰረተ ልማት ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን አቶ ኃይለማርያም በመግለጫቸው አመላክተዋል።
በቀጣይም ዘርፉን የበለጠ ለማጠናከር የክልሉ መንግስት ምቹ ሁኔታዎችን እየፈጠረ ስለመሆኑ አብራርተዋል።
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል