በክልሉ ከቱሪዝሙ ዘርፍ ባለፉት 9 ወራት 925.6 ሚሊዮን ብር ተገኝቷል
ባለፉት 9 ወራት 925.6 ሚሊዮን ብር መገኘቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለፀ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊው አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ በሰጡት መግለጫ በበጀት ዓመቱ 33 ሺ 800 የውጭ ሀገር ቱሪስቶች ክልሉን ጎብኝተው 364 ሚሊዮን ብር ገቢ መገኘቱ ገልፀዋል፡፡
በአጠቃላይ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር ቱሪሰቶች ባለፉት 9 ወራት 925.6 ሚሊዮን ብር መገኘቱንም ኃላፊው አብራርተዋል።
ክልሉ ያለው ሰው ሰራሽ፣ ተፈጥሯዊና ባህላዊ አቅሞች ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ እንዲሆን እንዳደረገው ገልፀዋል፡፡
የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ አሁን ላይ ለመሰረተ ልማት ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን አቶ ኃይለማርያም በመግለጫቸው አመላክተዋል።
በቀጣይም ዘርፉን የበለጠ ለማጠናከር የክልሉ መንግስት ምቹ ሁኔታዎችን እየፈጠረ ስለመሆኑ አብራርተዋል።
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ