የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በጋሞ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከ5 ሚሊዮን ብር  ድጋፍ አደረገ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በጋሞ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከ5 ሚሊዮን ብር  ድጋፍ አደረገ

5መቶሺ ብር ግምት ያለው  የቁሳቁስ ድጋፍም ለዞኑ አበርክቷል

ሀዋሳ፡ መጋቢት 12/2018(ደሬቴድ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በጋሞ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ አደረገ።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ድጋፋን ለጋሞ ዞን አስተዳደር አስረክበዋል።

የተከሰተው አደጋ እጅግ ልብ ሰባሪ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉ ህዝብና መንግስት ለተጎጂዎች መፅናናትን ይመኛል ብለዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩና ልዑካቸው የ 5 ሚሊዮን ጥሬ ገንዘብና 5 መቶ ሺ ብር ግምት ያለው ደራሽ ቁሳቁስ ለዞኑ አስተዳደር አስረክበዋል።

የክልሉ መንግስተና ህዝብ ተፈናቃዮችን በማቋቋሙ ሂደት አብሮነቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በአደጋው ለተጎዱ ወገኖች በሁሉም አቅጣጫ እየተደረገ ያለውን ርብርብ አድንቀው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።

አደጋው ከፍ ያለ ጉዳት በማስከተሉ ድጋፉ ተጠናክሮ መቀጠል አለበትም ብለዋል፡፡

ዘጋቢ:-ባዬ በልስቲ