የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በጋሞ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
5መቶሺ ብር ግምት ያለው የቁሳቁስ ድጋፍም ለዞኑ አበርክቷል
ሀዋሳ፡ መጋቢት 12/2018(ደሬቴድ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በጋሞ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ አደረገ።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ድጋፋን ለጋሞ ዞን አስተዳደር አስረክበዋል።
የተከሰተው አደጋ እጅግ ልብ ሰባሪ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉ ህዝብና መንግስት ለተጎጂዎች መፅናናትን ይመኛል ብለዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩና ልዑካቸው የ 5 ሚሊዮን ጥሬ ገንዘብና 5 መቶ ሺ ብር ግምት ያለው ደራሽ ቁሳቁስ ለዞኑ አስተዳደር አስረክበዋል።
የክልሉ መንግስተና ህዝብ ተፈናቃዮችን በማቋቋሙ ሂደት አብሮነቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በአደጋው ለተጎዱ ወገኖች በሁሉም አቅጣጫ እየተደረገ ያለውን ርብርብ አድንቀው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
አደጋው ከፍ ያለ ጉዳት በማስከተሉ ድጋፉ ተጠናክሮ መቀጠል አለበትም ብለዋል፡፡
ዘጋቢ:-ባዬ በልስቲ

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ
በዳውሮ ዞን ገና ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና የፓርቲ ምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሄደ