የቤንች ሸኮ ዞን ለሱማሌ ክልል ከ20ሺ በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የደን ችግኞች በስጦታ አበረከተ
በዞኑ በሐምሌ 10 በአንድ ጀንበር 10 ሚሊየን ችግኝ እንደሚተከልም ተጠቁሟል።
በዞኑ ግብርና መምሪያ የተፈጥሮ ደን እና አከባቢ ጥበቃ ዘርፍ አስተባባሪ እና ምክትል መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎጁ ኮይሳ እንደ ሀገር በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ከተያዘው እቅድ ውስጥም በቤንች ሸኮ ዞን ብቻ 10 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል መታቀዱን የተናገሩት ኃላፊው እስካሁንም 6 ሚሊየን 6 መቶ ሺ ጉድጓዶች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው 135 ሺ 392 የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተናግረዋል።
ተግባሩንም ለማስፈጸም በሁሉም አደረጃጀቶች ተገቢውን ቅስቀሳ መደረጉን እና ተከላውም 164 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት እንደሚሸፍንም ገልጸዋል።
የሚተከሉ ችግኞች ከመደበኛ የደኝ ችግኝ ባለፈም ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞችም እንደሚተከሉም ተናግረዋል።
ዞኑ ከ20 ሺ በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የደን ችግኞች ለሱማሌ ክልል በስጦታ ማበርከቱንም አቶ ጎጁ ተናግርዋል ፡፡
ዘጋቢ ፡ አብዮት በቀለ ከሚዛን ጣቢያችን
More Stories
በክረምት የተከናወኑ የወጣቶች በጎ ተግባራት ከ180 ሚሊየን ብር በላይ ከመንግስት ሊወጣ የነበረ ወጪ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የአርሶ አደሩን ገቢና የኑሮ ደረጃ በመሠረታዊነት ለማሻሻል በመንግሥት የተጀመሩ ሀገራዊ የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቮችን ማጠናከርና በግብርና ልማት ዘርፍ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ
ለይርጋጨፌ ከተማ የፈርጅ 1 እውቅና ተሰጠ