የቤንች ሸኮ ዞን ለሱማሌ ክልል ከ20ሺ በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የደን ችግኞች በስጦታ አበረከተ
በዞኑ በሐምሌ 10 በአንድ ጀንበር 10 ሚሊየን ችግኝ እንደሚተከልም ተጠቁሟል።
በዞኑ ግብርና መምሪያ የተፈጥሮ ደን እና አከባቢ ጥበቃ ዘርፍ አስተባባሪ እና ምክትል መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎጁ ኮይሳ እንደ ሀገር በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ከተያዘው እቅድ ውስጥም በቤንች ሸኮ ዞን ብቻ 10 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል መታቀዱን የተናገሩት ኃላፊው እስካሁንም 6 ሚሊየን 6 መቶ ሺ ጉድጓዶች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው 135 ሺ 392 የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተናግረዋል።
ተግባሩንም ለማስፈጸም በሁሉም አደረጃጀቶች ተገቢውን ቅስቀሳ መደረጉን እና ተከላውም 164 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት እንደሚሸፍንም ገልጸዋል።
የሚተከሉ ችግኞች ከመደበኛ የደኝ ችግኝ ባለፈም ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞችም እንደሚተከሉም ተናግረዋል።
ዞኑ ከ20 ሺ በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የደን ችግኞች ለሱማሌ ክልል በስጦታ ማበርከቱንም አቶ ጎጁ ተናግርዋል ፡፡
ዘጋቢ ፡ አብዮት በቀለ ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
ወጣቶች በዞኑ የሚገኙ ጸጋዎችን ተጠቅመው የገቢ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ገለጸ
በያዝነው ዓመት አስከ ጥቅምት ወር ድረስ 2 መቶ 50 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መላኩን የባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
የምርምር ተቋማት ከዝናብ ጥገኝነት ተላቀው የግብርናውን ስራ ውጤታማ እንዲያደርጉ የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ስራ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ኢንስቲትዩት አስታወቀ