የቤንች ሸኮ ዞን ለሱማሌ ክልል ከ20ሺ በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የደን ችግኞች በስጦታ አበረከተ
በዞኑ በሐምሌ 10 በአንድ ጀንበር 10 ሚሊየን ችግኝ እንደሚተከልም ተጠቁሟል።
በዞኑ ግብርና መምሪያ የተፈጥሮ ደን እና አከባቢ ጥበቃ ዘርፍ አስተባባሪ እና ምክትል መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎጁ ኮይሳ እንደ ሀገር በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ከተያዘው እቅድ ውስጥም በቤንች ሸኮ ዞን ብቻ 10 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል መታቀዱን የተናገሩት ኃላፊው እስካሁንም 6 ሚሊየን 6 መቶ ሺ ጉድጓዶች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው 135 ሺ 392 የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተናግረዋል።
ተግባሩንም ለማስፈጸም በሁሉም አደረጃጀቶች ተገቢውን ቅስቀሳ መደረጉን እና ተከላውም 164 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት እንደሚሸፍንም ገልጸዋል።
የሚተከሉ ችግኞች ከመደበኛ የደኝ ችግኝ ባለፈም ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞችም እንደሚተከሉም ተናግረዋል።
ዞኑ ከ20 ሺ በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የደን ችግኞች ለሱማሌ ክልል በስጦታ ማበርከቱንም አቶ ጎጁ ተናግርዋል ፡፡
ዘጋቢ ፡ አብዮት በቀለ ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
የብራይት ፕሮጀክት የሴቶችንና ህፃናትን የስራ ጫና ከማቃለል ባሻገር የንፁህ መጠጥ ውሀ ተደራሽነት ላይ የሚመታይ ተግባር ማከናወኑን የጋሞ ዞን ውሀና ኢነርጂ መምሪያ አስታወቀ
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ጥናታቸው በተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች ላይ ያተኮረ የማረጋገጫ ወርክሾፕ እና የርክክብ መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል
የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት የቤት ልማት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ