የቤንች ሸኮ ዞን ለሱማሌ ክልል ከ20ሺ በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የደን ችግኞች በስጦታ አበረከተ
በዞኑ በሐምሌ 10 በአንድ ጀንበር 10 ሚሊየን ችግኝ እንደሚተከልም ተጠቁሟል።
በዞኑ ግብርና መምሪያ የተፈጥሮ ደን እና አከባቢ ጥበቃ ዘርፍ አስተባባሪ እና ምክትል መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎጁ ኮይሳ እንደ ሀገር በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ከተያዘው እቅድ ውስጥም በቤንች ሸኮ ዞን ብቻ 10 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል መታቀዱን የተናገሩት ኃላፊው እስካሁንም 6 ሚሊየን 6 መቶ ሺ ጉድጓዶች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው 135 ሺ 392 የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተናግረዋል።
ተግባሩንም ለማስፈጸም በሁሉም አደረጃጀቶች ተገቢውን ቅስቀሳ መደረጉን እና ተከላውም 164 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት እንደሚሸፍንም ገልጸዋል።
የሚተከሉ ችግኞች ከመደበኛ የደኝ ችግኝ ባለፈም ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የፍራፍሬ ችግኞችም እንደሚተከሉም ተናግረዋል።
ዞኑ ከ20 ሺ በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የደን ችግኞች ለሱማሌ ክልል በስጦታ ማበርከቱንም አቶ ጎጁ ተናግርዋል ፡፡
ዘጋቢ ፡ አብዮት በቀለ ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
የግብርና ምርት ላይ የሚደረጉ ህገወጥ የዋጋ ጭማሪዎችን ለመከላከልና ለማረም ሸማቾች ከመንግስት ጋር በቅንጅት ሊስራ እንደሚገባ ተገለጸ
የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት መንግስት የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የአርባምንጭ ከተማ ሸማቾችና ነጋዴዎች ጠየቁ
ባንኩ አዳዲስ የዲጂታል አገልግሎቶች መጀመሩን አስታወቀ