ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ በመመዝገብ የሚፈልገውን የፖለቲካ ፓርቲ እንዲመርጥ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ጥሪ አቀረበ
ፓርቲው በምርጫ ስነ-ምግባር ዙሪያ ከእጩዎቹ እና አመራሩ ጋር ውይይት በሚዛን አማን ከተማ አካሂዷል።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) በቤንች ሸኮ ዞን በሚዛን አማን ከተማ ከእጩዎቹ እና ከአመራሩ ጋር ባደረገው የምርጫ ስነ-ምግባር ውይይት ላይ የቤንች ሸኮ እና የሸካ ዞን ኢዜማ አስተባባሪው አቶ ተፈራ በዛብህ እንደተናገሩት፤ በሁለቱ ዞኖች ለተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤት አባላት ምርጫ እጩዎቻቸውን ለምርጫው ለማቅረብ ተዘጋጅተዋል።
ለምርጫው ሂደትም ህብረተሰቡ ከወዲሁ በመውጣት በመመዝገብ ካርድ መያዝ ይገባቸዋልም ብለዋል።
ምርጫው ነጻ፣ ፍትሀዊ ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን ከአባሎቻቸው ጋር በምርጫ ስነ-ምግባር ውይይት ማድረጋቸውንም ነው የተናገሩት።
ሰላም ከምንም በላይ አስፈላጊ ነው ያሉት አቶ ተፈራ፤ ሰላማዊ ምርጫ እንዲካሄድ እና ሰላምን በማስጠበቅ ረገድ ፓርቲያቸው እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
የሚዛን ምርጫ ክልል ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋር ምክር ቤት ሰብሳቢ እና የኢዜማ ሰብሳቢ አቶ ብርሀኑ ገብረመድህን በበኩላቸው፤ በሚዛን ምርጫ ክልል ፓርቲያቸው ኢዜማ አንድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና አስር የክልል ምክር ቤት አጩዎችን ለምርጫ ማዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።
ምርጫው ነጻ፣ ፍትሀዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር እየሰሩ መሆኑን ጠቁመው ህዝቡም በነቂስ በመውጣት ተመዝግቦ ካርድ በመውሰድ የሚፈልገውን ፓርቲ በድምጹ ማረጋገጥ ይገባዋል ብለዋል።
ከአባሎቻቸው መካከል አቶ ጋሻው አዲሱ እና መምህርት ማስረሻ ጥላሁን እንዲሁም መምህርት ባንቺአየሁ በላይ እንደተናገሩት ምርጫው ነጻ፣ ፍትሀዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ ጠቁመዋል።
ህብረተሰቡም በምርጫ ምዝገባ ወቅት በመውጣት በመመዝገብ ድምጹን ለሚፈልገው ፓርቲ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።
ሰላም በማስጠበቅ ረገድም የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ: አብዮት በቀለ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ