በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብዝሃ ባህል፣ ታሪክና እሴትን ለመገንባት በተሠሩ ስራዎች በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለፀ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብዝሃ ባህል፣ ታሪክና እሴትን ለመገንባት በተሠሩ ስራዎች በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለፀ

ይህ የተገለፀው “በባህልና ቱሪዝም እምርታ ለክልላችን ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የሴክተር ጉባኤ በሳጃ ከተማ እየተከናወነ ባለበት ወቅት ነው።

በጉባኤው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሄረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ገመቹ አረቦ፣ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ አቶ ሳሙኤል መንገሻ፣ የክልሉ ምክር ቤት የማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ እንዳልካቸው ጌታቸው፣ የክልሉ የአመራር አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ብላቱ፣ የየም ዞን የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አብርሀም ዝናብ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በጉባኤው የ2018 ዕቅድ አፈፃፀም እና የ2019 ጠቋሚ ዕቅድ ዋና ዋና ግቦች ቀርበው ውይይት እየተደረ ነው።

ዘጋቢ፡ ፉኣድ አብደላ – ከወልቂጤ ጣቢያችን