የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራት የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን ተወያይቶ አፀደቀ
ሀዋሳ: ጥር 26/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀኑ አራት የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን ተወያይቶ በሙሉ ድምፅ ተቀብሎ አፅድቋል።
በዚህ መሠረት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ገቢ ግብር አዋጅ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የኤክሳይዝ ታክስ ረቂቅ አዋጅ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የጫት ኤክሳይዝ ታክስ ረቂቅ አዋጅ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋም እና እውቅና ለመስጠት የወጣ ረቂቅ አዋጅ የሚሉት መሆናቸዉ ተመልክቷል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የመሠረተ ልማት ችግሮችን ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተገለጸ
በአከባቢዉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር እጥረት ችግር ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው
የአከባቢን እና የሀገርን ሰላም ለማረጋገጥ የሚቻለው ህብረተሰቡን የሰላም ባለቤት ማድረግ ሲቻል መሆኑ ተገለጸ