የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራት የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን ተወያይቶ አፀደቀ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራት የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን ተወያይቶ አፀደቀ

ሀዋሳ: ጥር 26/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀኑ አራት የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን ተወያይቶ በሙሉ ድምፅ ተቀብሎ አፅድቋል።

በዚህ መሠረት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ገቢ ግብር አዋጅ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የኤክሳይዝ ታክስ ረቂቅ አዋጅ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የጫት ኤክሳይዝ ታክስ ረቂቅ አዋጅ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋም እና እውቅና ለመስጠት የወጣ ረቂቅ አዋጅ የሚሉት መሆናቸዉ ተመልክቷል።

ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ