በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የፕላን መሰረተ ልማት እና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአርባ ምንጭ ከተማ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት የተከናወኑ ተግባራትን የመስክ ምልከታ አደረገ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የፕላን መሰረተ ልማት እና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአርባ ምንጭ ከተማ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት የተከናወኑ ተግባራትን የመስክ ምልከታ አደረገ

‎በመስክ ምልከታው የአርባ ምንጭ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ሽመልስ ታደሰ እና የሶስቱም ዘርፋ ቋሚ ኮሚቴዎች ተገኝተዋል።

‎በ2018 በጀት አመት በ6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት፣ የመሰረተ ልማት አውታሮች፣ የመልካም አስተዳደር እና መንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የቅርብ ክትትል እና ምልከታ ተደርጓል።

‎በምልከታው ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የገነባው የአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት እና ዲች፣ የክፍለ ከተማ ቢሮ ግንባታ፣ የመንገድ ከፈታ እና የመንገድ ዳር መብራት ዝርጋታ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ድጋፍ የተሰራው የኮሪደር ልማቱ አካል የሆነው ዘመናዊ መፀዳጃ ግንባታና ሌሎችም ዘላቂ የልማት ስራዎች ተገምግመዋል።

‎በአርባምንጭ ከተማ በ6 ወራት ለ55 ማህበራት የመኖሪያ ቤት ቦታ የተሰጠ ሲሆን ከእነዚህም 15 ማህበራት ምንም አይነት ግንባታ ያላከናወኑ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው ርምጃ እንደሚወሰድም አስታውቀዋል።

‎በመስክ ምልከታው በትራንስፖርትና ሎጂስቲክ አገልግሎት አሰጣጥ፣ የስራ እድል ፈጣራና የገበያ ትስስር አንፃር ከታዩ ዘርፎች አንዱና የግብርናው ዘርፍ እምርታዎች የሆኑ በንብ ማነብ ስራ ላይ የተደራጁ ማህበራት፣ የወተትና የዶሮ መንደሮች ሼድ ግንባታ እንዲሁም የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ፤ በእንጨት ስራ ሽግግር ያደረጉ ማህበራትን መመልከት ተችሏል።

‎የክልሉ ምክር ቤት የፕላንና መሰረተ ልማትና የመንግሥት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አቶ እንቁ ዮሐንስ፣ የአርባምንጭ ከተማ የህዝብ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ሽመልስ ታደሰን ጨምሮ የዘርፉ ኃላፊዎች እና የሶስቱም ዘርፋ ቋሚ ኮሚቴዎች ተገኝተዋል።

‎ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን