ባለፉት ስድስት ወራት ከ7 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ እርሳሱ አሰፋ፤ ከተማው በርካታ ምርት የሚመረትበትና የንግድ ማዕከል ቢሆንም ከዚህ ቀደም ገቢን ከመሰብሰብ አኳያ ጠንካራ እንዳልነበር አንስተዋል።
ይሁን እንጂ ችግሩን ለመፍታት በተሠራው ሥራ አፈፃፀሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እንደሚገኝ የገለጹት ኃላፊው፤ ዘንድሮ በግማሽ በጀት ዓመቱ ብቻ ከአምናው ሙሉ ዓመት የተሻለ ገቢ መሰብሰቡን ነው ያስረዱት።
ባለሙያዎች ከተጣለባቸው ኃላፊነት አንፃር ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ ማድረግ፣ ሁሉም የአመራር አካላት የገቢ ሥራን በባለቤትነት እንዲደግፍ ማድረግ፣ ህገወጥ የገቢ ስወራ ላይ ያለውን ቁጥጥር ማጥበቅ፣ መንግሥት ያወጣዉን አዋጅ በጥብቅ ዲሲፕሊን ተፈፃሚ እንዲሆን ማድረግና የመሳሰሉት ከተሠሩ ሥራዎች ለአብነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።
በበጀት ዓመቱ በመደበኛና ማዘጋጃ ቤት 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ በግማሽ ዓመቱ 7 መቶ 15 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን ነው አቶ እርሳሱ ያስረዱት።
ዘጋቢ፡ አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ባለፉት ስድስት ወራት ከ7 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል