ባለፉት ስድስት ወራት ከ7 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ እርሳሱ አሰፋ፤ ከተማው በርካታ ምርት የሚመረትበትና የንግድ ማዕከል ቢሆንም ከዚህ ቀደም ገቢን ከመሰብሰብ አኳያ ጠንካራ እንዳልነበር አንስተዋል።
ይሁን እንጂ ችግሩን ለመፍታት በተሠራው ሥራ አፈፃፀሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እንደሚገኝ የገለጹት ኃላፊው፤ ዘንድሮ በግማሽ በጀት ዓመቱ ብቻ ከአምናው ሙሉ ዓመት የተሻለ ገቢ መሰብሰቡን ነው ያስረዱት።
ባለሙያዎች ከተጣለባቸው ኃላፊነት አንፃር ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ ማድረግ፣ ሁሉም የአመራር አካላት የገቢ ሥራን በባለቤትነት እንዲደግፍ ማድረግ፣ ህገወጥ የገቢ ስወራ ላይ ያለውን ቁጥጥር ማጥበቅ፣ መንግሥት ያወጣዉን አዋጅ በጥብቅ ዲሲፕሊን ተፈፃሚ እንዲሆን ማድረግና የመሳሰሉት ከተሠሩ ሥራዎች ለአብነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።
በበጀት ዓመቱ በመደበኛና ማዘጋጃ ቤት 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ በግማሽ ዓመቱ 7 መቶ 15 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን ነው አቶ እርሳሱ ያስረዱት።
ዘጋቢ፡ አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ባለፉት ስድስት ወራት ከ7 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ