ባለፉት ስድስት ወራት ከ7 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ እርሳሱ አሰፋ፤ ከተማው በርካታ ምርት የሚመረትበትና የንግድ ማዕከል ቢሆንም ከዚህ ቀደም ገቢን ከመሰብሰብ አኳያ ጠንካራ እንዳልነበር አንስተዋል።
ይሁን እንጂ ችግሩን ለመፍታት በተሠራው ሥራ አፈፃፀሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እንደሚገኝ የገለጹት ኃላፊው፤ ዘንድሮ በግማሽ በጀት ዓመቱ ብቻ ከአምናው ሙሉ ዓመት የተሻለ ገቢ መሰብሰቡን ነው ያስረዱት።
ባለሙያዎች ከተጣለባቸው ኃላፊነት አንፃር ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ ማድረግ፣ ሁሉም የአመራር አካላት የገቢ ሥራን በባለቤትነት እንዲደግፍ ማድረግ፣ ህገወጥ የገቢ ስወራ ላይ ያለውን ቁጥጥር ማጥበቅ፣ መንግሥት ያወጣዉን አዋጅ በጥብቅ ዲሲፕሊን ተፈፃሚ እንዲሆን ማድረግና የመሳሰሉት ከተሠሩ ሥራዎች ለአብነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።
በበጀት ዓመቱ በመደበኛና ማዘጋጃ ቤት 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ በግማሽ ዓመቱ 7 መቶ 15 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን ነው አቶ እርሳሱ ያስረዱት።
ዘጋቢ፡ አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ባለፉት ስድስት ወራት ከ7 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ

More Stories
አንትሮሽት የእናቶች የምስጋና በዓል ለትውልድ እንዲተላለፍ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የአርባምንጭ ማረሚያ ተቋም የህብረ ብሔራዊነት ማሳያ እና የምርታማ ዜጋ ማፍሪያ ተቋም ነው – ኮሚሽነር ብርቱካን መንግስቱ
በተጀመረው የተፋሰስ ዘመቻ ሥነ ህይወታዊና ሥነ አካላዊ የአፈርና ውሃ ጥበቃን በማጠናከር የአረንጓዴ አሻራችንን ራዕይ መደገፍ እነደሚገባ ተገለጸ