ባለፉት ስድስት ወራት ከ7 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ
የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ እርሳሱ አሰፋ፤ ከተማው በርካታ ምርት የሚመረትበትና የንግድ ማዕከል ቢሆንም ከዚህ ቀደም ገቢን ከመሰብሰብ አኳያ ጠንካራ እንዳልነበር አንስተዋል።
ይሁን እንጂ ችግሩን ለመፍታት በተሠራው ሥራ አፈፃፀሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ እንደሚገኝ የገለጹት ኃላፊው፤ ዘንድሮ በግማሽ በጀት ዓመቱ ብቻ ከአምናው ሙሉ ዓመት የተሻለ ገቢ መሰብሰቡን ነው ያስረዱት።
ባለሙያዎች ከተጣለባቸው ኃላፊነት አንፃር ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ ማድረግ፣ ሁሉም የአመራር አካላት የገቢ ሥራን በባለቤትነት እንዲደግፍ ማድረግ፣ ህገወጥ የገቢ ስወራ ላይ ያለውን ቁጥጥር ማጥበቅ፣ መንግሥት ያወጣዉን አዋጅ በጥብቅ ዲሲፕሊን ተፈፃሚ እንዲሆን ማድረግና የመሳሰሉት ከተሠሩ ሥራዎች ለአብነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።
በበጀት ዓመቱ በመደበኛና ማዘጋጃ ቤት 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ በግማሽ ዓመቱ 7 መቶ 15 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን ነው አቶ እርሳሱ ያስረዱት።
ዘጋቢ፡ አማኑኤል ትዕግስቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ባለፉት ስድስት ወራት ከ7 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ