ሀዋሳ፡ ጥር 13/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ፍትህ ቢሮ በክልሉ ለሚገኙ አቃቢያነ ህግ በተሻሻለው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
የክልሉ ፍትህ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ጤናሁን ጨርቆስ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በተለይም የተሻሻለው አዲሱ የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 ቀደም ሲል በፍትህ ስርዓት ላይ እንደጉድለት የሚነሱ ችግሮችን የሚቀርፍና በደረጃ አወሳሰንና እርከን ላይ መሻሻልን ያስቀመጠ እንደሆነ አብራርተዋል።
የዘርፉ ባለሙያዎች ከወቅቱ ጋር የሚሄድ አሰራር እየተከተሉ አዋጆችን በተገቢው በመረዳት መፈፀም እንደሚገባ ያስረዱት ምክትል ቢሮ ኃላፊው በአቃቢያነ ህግ ስነ ምግባር ደንብ መሠረት መተግበር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
አዲሱ የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 ቀደም ሲል በነበረው አዋጅ ውስጥ ጉድለት የነበሩ ጉዳዮችን የሚቀርፍና በህብረተሰቡ ዘንድ አስተማሪ አይደሉም የሚባሉ ውሳኔዎችን የሚያሻሽል እንደሆነ አስረድተዋል።
አክለውም ባለሙያዎች ባገኙት ዕውቀት ታግዘው ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን ይገባል ብለዋል።
የተከለሰው የቅጣት አወሳሰን መመሪያ ትክክለኛነት እና ወጥነትን በሚያረጋግጥ አግባብ ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
ሕዝቡ ከየትኛውም የወንጀል ስጋት ነጻ እንዲሆንና ወንጀል የፈጸሙም ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ያደርጋል ብለዋል።
ሁሉም ኃላፊነቱን ከተወጣ የፍትሕ ሥርዓቱን በሕዝብ የታመነ እና የሕግ የበላይነት የተረጋገጠበት ማድረግ ስለሚቻል ይህ እውን እንዲሆን ሁሉም የፍትሕ አካላት ኃላፊነት እንዳለባቸው አንስተዋል።
ዘጋቢ፡ አይናለም ሰለሞን – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ