የበአሉን አከባበር የማጠቃለያ ግምገማና ለሚዲያዎች የዕውቅና መርሀ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ ተከናውኗል።
በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፤ በዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦች በዓል የመገናኛ ብዙሀን ዘጋቢ ፊልሞችን በማዘጋጀት የቀጥታ ስርጭት በመስራትና ልዩ ልዩ ዘገባዎችን ለህዝቡ በማድረስ ሚናቸውን ተወጥተዋል ብለዋል።
በተለይ ከለውጡ ማግስት የተከበሩ ሁሉም በዓላት ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ከፍ ያለ ሚና ተጫውተዋል ነው ያሉት።
የለውጡ ፍሬ በሆነው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በዓሉ መከበሩም የዚሁ ማሳያ ስለመሆኑ አመላክተዋል።
በዓሉ ክብሩን ጠብቆና ህብረ ብሔራዊነትን በሚያሳይ መልኩ እንዲከበር አዲሱ ክልል የሰራው ተግባር ከመቼውም በላይ የሚደነቅ መሆኑን አፈ ጉባኤው አመላክተዋል።
በዓሉ አላማውን ያሳካ እንዲሆን የበኩላቸውን ለተወጡ ምስጋና ያቀረቡት አቶ አገኘሁ፤ ለሚዲያ አካላትም ምስጋናና ዕውቅና ሰጥተዋል።
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
የሚዲያ ተቋማትና ባለሙያዎች የመረጃ ተደራሽነትን በማዘመን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማረም የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው ተገለጸ
በማርበርግ ቫይረስ በሽታ ቤተሰቦቻቸውን ላጡ ወገኖች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተጠቆመ
ስፖርተኞች መልካም ስብእና ተላብሰው ውድድራቸውን እያካሄዱ እንደሚገኙ የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ አስታወቀ