የበአሉን አከባበር የማጠቃለያ ግምገማና ለሚዲያዎች የዕውቅና መርሀ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ ተከናውኗል።
በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፤ በዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦች በዓል የመገናኛ ብዙሀን ዘጋቢ ፊልሞችን በማዘጋጀት የቀጥታ ስርጭት በመስራትና ልዩ ልዩ ዘገባዎችን ለህዝቡ በማድረስ ሚናቸውን ተወጥተዋል ብለዋል።
በተለይ ከለውጡ ማግስት የተከበሩ ሁሉም በዓላት ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ከፍ ያለ ሚና ተጫውተዋል ነው ያሉት።
የለውጡ ፍሬ በሆነው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በዓሉ መከበሩም የዚሁ ማሳያ ስለመሆኑ አመላክተዋል።
በዓሉ ክብሩን ጠብቆና ህብረ ብሔራዊነትን በሚያሳይ መልኩ እንዲከበር አዲሱ ክልል የሰራው ተግባር ከመቼውም በላይ የሚደነቅ መሆኑን አፈ ጉባኤው አመላክተዋል።
በዓሉ አላማውን ያሳካ እንዲሆን የበኩላቸውን ለተወጡ ምስጋና ያቀረቡት አቶ አገኘሁ፤ ለሚዲያ አካላትም ምስጋናና ዕውቅና ሰጥተዋል።
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ